
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 18/2017(ኢዜአ)፦ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ዘላቂና አካታች የፋይናንስና የኢንሹራንስ ስርዓትን ለመገንባት ትልቅ ሚና እየተጫወተ መሆኑን የብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ ገለፁ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት 51ኛው የአፍሪካ ኢንሹራንስ ድርጅት ዓመታዊ ኮንፍረንስ እና ጠቅላላ ጉባኤ በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ነው።
የብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያን ጨምሮ በብዙ የአፍሪካ ሀገራት የኢኮኖሚ ሪፎርም እየተከናወነ ነው።

ብድርን በተመለከተ ያሉ ችግሮች ሲፈቱ የኢንሹራንስ ዘርፉን በሚፈለገው አቅም ማሳደግ እንደሚቻልም ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ እየተከናወነ ያለው የኢኮኖሚ ሪፎርም የግሉን ዘርፍ በሚያበረታታና ኢንቨስትመንትን በሚያረጋግጥ መልኩ በልዩ አመራር እየተተገበረ መሆኑን አንስተዋል።
የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ትግበራ በፋይናንስ ዘርፉ ዘላቂ የኢኮኖሚ እድገትን የሚያረጋግጥ ተስፋ ሰጪ ውጤት እያሳየ ነውም ብለዋል።
በፋይናንስ ዘርፉ ህግ ከማሻሻል ጀምሮ በኢኮኖሚው ላይ ትርጉም ያለው ለውጥ የሚያመጡ የአሰራር ሪፎርሞች መከናወናቸውን ጨምረው ተናግረዋል።

ባለፉት የለውጥ ዓመታት በፋይናንስ ዘርፉ የተሰሩ አጠቃላይ ስራዎች የኢንሹራንስ ዘርፉን ዕድገት በማገዝ በኩል ሰፊ አስተዋጽኦ እንዳላቸው ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ እየተከናወነ ያለው የዲጂታል ሽግግር በአጠቃላይ ኢኮኖሚያዊ ለውጥን ለማምጣትና የኢንሹራንስ ዘርፉን ውጤታማ ለማድረግ ከፍተኛ አበርክቶ እንዳለውም ጠቁመዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026