
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 18/2017(ኢዜአ)፦ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ዘላቂና አካታች የፋይናንስና የኢንሹራንስ ስርዓትን ለመገንባት ትልቅ ሚና እየተጫወተ መሆኑን የብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ ገለፁ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት 51ኛው የአፍሪካ ኢንሹራንስ ድርጅት ዓመታዊ ኮንፍረንስ እና ጠቅላላ ጉባኤ በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ነው።
የብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያን ጨምሮ በብዙ የአፍሪካ ሀገራት የኢኮኖሚ ሪፎርም እየተከናወነ ነው።

ብድርን በተመለከተ ያሉ ችግሮች ሲፈቱ የኢንሹራንስ ዘርፉን በሚፈለገው አቅም ማሳደግ እንደሚቻልም ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ እየተከናወነ ያለው የኢኮኖሚ ሪፎርም የግሉን ዘርፍ በሚያበረታታና ኢንቨስትመንትን በሚያረጋግጥ መልኩ በልዩ አመራር እየተተገበረ መሆኑን አንስተዋል።
የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ትግበራ በፋይናንስ ዘርፉ ዘላቂ የኢኮኖሚ እድገትን የሚያረጋግጥ ተስፋ ሰጪ ውጤት እያሳየ ነውም ብለዋል።
በፋይናንስ ዘርፉ ህግ ከማሻሻል ጀምሮ በኢኮኖሚው ላይ ትርጉም ያለው ለውጥ የሚያመጡ የአሰራር ሪፎርሞች መከናወናቸውን ጨምረው ተናግረዋል።

ባለፉት የለውጥ ዓመታት በፋይናንስ ዘርፉ የተሰሩ አጠቃላይ ስራዎች የኢንሹራንስ ዘርፉን ዕድገት በማገዝ በኩል ሰፊ አስተዋጽኦ እንዳላቸው ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ እየተከናወነ ያለው የዲጂታል ሽግግር በአጠቃላይ ኢኮኖሚያዊ ለውጥን ለማምጣትና የኢንሹራንስ ዘርፉን ውጤታማ ለማድረግ ከፍተኛ አበርክቶ እንዳለውም ጠቁመዋል።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026