
ሀዋሳ፤ግንቦት 20/2017( ኢዜአ)፦በሀዋሳ ከተማ እየተገነባ ያለው ሁለተኛው ምእራፍ የ5 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ስራ በመገባደድ ላይ መሆኑን የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ አስታወቁ።
ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ፤ የሁለተኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ስራ ያለበትን ደረጃ እና አጠቃላይ ክንውኑን ተመልክተዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንደገለጹት፥የልማት ስራዎችን መጀመር ብቻ ሳይሆን በጥራትና በፍጥነት የማጠናቀቅ ልምድ እየዳበረ መጥቷል።
አሁን ላይ የአስፋልት ንጣፍ በመከናወን ላይ እንደሚገኝ ጠቁመው፥ ግንባታው በተያዘለት ጊዜ በጥራትና በፍጥነት በመገባደድ ላይ ይገኛል ብለዋል።
የግንባታው ስኬት የክልሉ መንግስት በየደረጃው ያሉ አመራሮችና የከተማው ህዝብ የትብብርና እገዛ ድምር ውጤት መሆኑን ተናግረዋል።
ሀዋሳ በተለገሳት ተፈጥሮና በነዋሪዎቿ ብርቱ ጥረት እድገቷና ውበቷ ይበልጥ እየፈካ መሆኑን ተናግረው፥ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማትም ወደ ላቀ ምዕራፍ የሚያሸጋግራት ይሆናል ብለዋል።
የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ መኩሪያ መርሻዬ፥የመጀመሪያው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ሥራ በጥራትና በተያዘለት ጊዜ ተጠናቆ ለአገልግሎት መብቃቱን አንስተዋል።
የሁለተኛው ምዕራፍ ግንባታ ደግሞ በጥራትና በፍጥነት በተሻለ መልኩ በመከናወን ላይ መሆኑን ጠቁመው፥በአጭር ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃል ብለዋል።
የፕሮጀክቱን አፈፃፀም በጥራትና በተሻለ ፍጥነት ለማጠናቀቅ የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት የድጋፍና የክትትል ሥራውን አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።
የግንባታ ስራውን እያከናወነ ያለው ይርጋዓለም ኮንስትራክሽን ባለቤት ኢንጂነር ዘላለም ወልደአማኑኤል፥የፕሮጀክት ሥራው በጥራትና በፍጥነት ሌት ከቀን እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
የግንባታ ስራው የኮንክሪት አስፋልት፣ የፍሳሽ፣ የእግረኛና ብስክሌት መንገድ፣ የአረንጓዴ ልማትና ሌሎችም ከተማዋን የሚያዘምኑ እና የሚያስውቡ ስራዎችን ያካተተ መሆኑን ጠቁመው፥በአጭር ጊዜ ውስጥ የሚጠናቀቅ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026