ሆሳዕና፤ግንቦት 21/2017 (ኢዜአ)፦በሆሳዕና ከተማ የመጀመሪያ ምዕራፍ 24 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የኮሪደር ልማት ስራን በፍጥነት ለማጠናቀቅ እየተሰራ እንደሚገኝ የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ አቶ ዳዊት ጡምደዶ ገለጹ፡፡
አቶ ዳዊት ጡምደዶ ለኢዜአ እንደገለፁት፥የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በመንግሥት ልዩ ትኩረት ከተሰጡ የልማት ስራዎች አንዱ የኮሪደር ልማት ስራ ነው፡፡
በከተማው በጥቅሉ 35 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ስራ ለማከናወን ታቅዶ ወደ ተግባር መገባቱን አንስተው፥ ከዚህ ውስጥ በመጀመሪያው ምዕራፍ የ24 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ስራ እየተፋጠነ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
አሁን ላይ የአፈር ሙሌትን ጨምሮ አብዛኛው ስራ ተጠናቆ ቴራዞ የማንጠፍ ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ጠቁመው፥ እስከሚቀጥለው ሰኔ ወር አጋማሽ ድረስ ባሉት ጊዜያት በማጠናቀቅ ወደ አገልግሎት እንዲገባ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
በከተማው የጀሎ ናረሞ ቀበሌ ነዋሪ ወይዘሮ ብዙአየሁ መሀመድ በከተማው እየተሰራ በሚገኘው የኮሪደር ልማት ስራ በፅዳት አጠባበቅና በእግረኛ መንገድ አጠቃቀም ዙሪያ የነበሩ ውስንነቶችን እየቀረፈ ስለመምጣቱም ጠቁመዋል፡፡
እንዲሁም ከተማዋን ለነዋሪዎችና ለእንግዶች ምቹ ከማድረግ አኳያ እየተሰራ ያለው ስራ ጥሩ በመሆኑ ለልማቱ የሚያደርጉትን አስተዋጽኦ እንደሚያጠናክሩም አረጋግጠዋል፡፡
በአስተዳደሩ የተጀመረው የኮሪደር ልማት ስራ ከተሞችን ውብና ፅዱ ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ ተስፋ ሰጪ ውጤት ማምጣቱን የገለፁት ደግሞ በከተማው ሄጦ ቀበሌ ነዋሪው አቶ አሰፋ ላዕዋሞ ናቸው።
ቀደም ሲል የከተማዋ መንገዶች ጠባብ በመሆናቸው ለትራፊክ አደጋ የሚያጋልጡ ሁኔታዎችን የኮሪደር ልማቱ እንደሚቀርፈው ገልጸዋል፡፡
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025