የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በሆሳዕና ከተማ 24 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የኮሪደር ልማት ስራ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው-ከንቲባ ዳዊት ጡምደዶ

May 30, 2025

IDOPRESS

ሆሳዕና፤ግንቦት 21/2017 (ኢዜአ)፦በሆሳዕና ከተማ የመጀመሪያ ምዕራፍ 24 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የኮሪደር ልማት ስራን በፍጥነት ለማጠናቀቅ እየተሰራ እንደሚገኝ የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ አቶ ዳዊት ጡምደዶ ገለጹ፡፡


አቶ ዳዊት ጡምደዶ ለኢዜአ እንደገለፁት፥የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በመንግሥት ልዩ ትኩረት ከተሰጡ የልማት ስራዎች አንዱ የኮሪደር ልማት ስራ ነው፡፡


በከተማው በጥቅሉ 35 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ስራ ለማከናወን ታቅዶ ወደ ተግባር መገባቱን አንስተው፥ ከዚህ ውስጥ በመጀመሪያው ምዕራፍ የ24 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ስራ እየተፋጠነ መሆኑን ተናግረዋል፡፡


አሁን ላይ የአፈር ሙሌትን ጨምሮ አብዛኛው ስራ ተጠናቆ ቴራዞ የማንጠፍ ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ጠቁመው፥ እስከሚቀጥለው ሰኔ ወር አጋማሽ ድረስ ባሉት ጊዜያት በማጠናቀቅ ወደ አገልግሎት እንዲገባ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡


በከተማው የጀሎ ናረሞ ቀበሌ ነዋሪ ወይዘሮ ብዙአየሁ መሀመድ በከተማው እየተሰራ በሚገኘው የኮሪደር ልማት ስራ በፅዳት አጠባበቅና በእግረኛ መንገድ አጠቃቀም ዙሪያ የነበሩ ውስንነቶችን እየቀረፈ ስለመምጣቱም ጠቁመዋል፡፡


እንዲሁም ከተማዋን ለነዋሪዎችና ለእንግዶች ምቹ ከማድረግ አኳያ እየተሰራ ያለው ስራ ጥሩ በመሆኑ ለልማቱ የሚያደርጉትን አስተዋጽኦ እንደሚያጠናክሩም አረጋግጠዋል፡፡


በአስተዳደሩ የተጀመረው የኮሪደር ልማት ስራ ከተሞችን ውብና ፅዱ ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ ተስፋ ሰጪ ውጤት ማምጣቱን የገለፁት ደግሞ በከተማው ሄጦ ቀበሌ ነዋሪው አቶ አሰፋ ላዕዋሞ ናቸው።


ቀደም ሲል የከተማዋ መንገዶች ጠባብ በመሆናቸው ለትራፊክ አደጋ የሚያጋልጡ ሁኔታዎችን የኮሪደር ልማቱ እንደሚቀርፈው ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ ነው-ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ

ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

May 21, 2026

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026