የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የጥናትና ምርምር ሥራዎች ሀገራዊ የልማት አቅጣጫን የሚያግዙና መፍትሄ ጠቋሚ መሆን አለባቸው

Jun 3, 2025

IDOPRESS

ወላይታ ሶዶ፤ ግንቦት 25/2017 (ኢዜአ)፡-ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚያከናውኗቸው የጥናትና ምርምር ሥራዎች ሀገራዊ የልማት አቅጣጫን የሚያግዙና ለችግሮች መፍትሄ ጠቋሚ መሆን እንዳለባቸው ተመለከተ።

በጉዳዩ ላይ አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡ ተመራማሪዎች መካከል የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የቦርድ አባል ፕሮፌሰር ዝናቡ ገብረማርያም እንዳሉት፣ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚካሄዱ የጥናትና የምርምር ሥራዎች ሀገራዊ የልማት እንቅስቃሴን የሚያሳልጡና ለማህበረሰቡ ችግሮች መፍትሄ ጠቋሚ መሆን አለባቸው።

በተለይ በመንግስት ትኩረት ተሰጥቶ የተለዩ ሀገራዊ የልማት እቅዶችን ለማስፈጸም የሚያግዙ መሆን እንደሚገባቸው ነው የገለጹ።

እንደሀገር ትኩረት በተሰጣቸው የልማት መስኮችና ትኩረቶች ላይ የምርምር ውጤቶች ለመንግስት በማቅረብ በተቀናጀ መንገድ መስራት ይገባል ሲሉም ነው የገለጹት።

የምሁራኑ የምርምር ሥራ የመንግስትን የልማትና የለውጥ ግቦች አቅጣጫ የሚጠቁሙ መሆን ይገባቸዋል ሲሉም ነው የገለጹት።


በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ የአፈር ምርምርና የእጽዋት ሥነ ምግብ ተመራማሪ ፕሮፌሰር ሸለመ በየነ በበኩላቸው፣ በዩኒቨርሲቲው የሚካሄዱ የጥናትና ምርምር ሥራዎች ለሀገር እድገት ከፍተኛ ድርሻ እያበረከቱ መሆናቸውን አስታውሰዋል።

የምርምር ውጤቶቹ ልማትን በዘላቂነት ለማጠናከር ካላቸው ፋይዳ በተጨማሪ የአርሶ አደሩን ጊዜ፣ ጉልበትና ወጪን ለመቆጠብ እንዳስቻሉ ገልጸዋል።

በተለይም በአካባቢ ያሉ የልማት አቅሞች በአግባቡ ጥቅም ላይ የሚውሉበትን አማራጭ ማቅረብ ላይ ትኩረት መሰጠት እንዳለበት ነው የገለጹት።

ለምርምር ስራዎች ውጤታማነት ቅንጅታዊ አሰራርን መዘርጋትና ለዘርፉ የተመደበ በጀትን በአግባቡ ሥራ ላይ ማዋል እንደሚገባም ፕሮፌሰር ሸለመ አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026

‎ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ተወዳዳሪነቷን ለማሳደግ ርብርብ እየተደረገ ነው 

‎ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...

Apr 20, 2026