
ወላይታ ሶዶ፤ ግንቦት 25/2017 (ኢዜአ)፡-ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚያከናውኗቸው የጥናትና ምርምር ሥራዎች ሀገራዊ የልማት አቅጣጫን የሚያግዙና ለችግሮች መፍትሄ ጠቋሚ መሆን እንዳለባቸው ተመለከተ።
በጉዳዩ ላይ አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡ ተመራማሪዎች መካከል የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የቦርድ አባል ፕሮፌሰር ዝናቡ ገብረማርያም እንዳሉት፣ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚካሄዱ የጥናትና የምርምር ሥራዎች ሀገራዊ የልማት እንቅስቃሴን የሚያሳልጡና ለማህበረሰቡ ችግሮች መፍትሄ ጠቋሚ መሆን አለባቸው።
በተለይ በመንግስት ትኩረት ተሰጥቶ የተለዩ ሀገራዊ የልማት እቅዶችን ለማስፈጸም የሚያግዙ መሆን እንደሚገባቸው ነው የገለጹ።
እንደሀገር ትኩረት በተሰጣቸው የልማት መስኮችና ትኩረቶች ላይ የምርምር ውጤቶች ለመንግስት በማቅረብ በተቀናጀ መንገድ መስራት ይገባል ሲሉም ነው የገለጹት።
የምሁራኑ የምርምር ሥራ የመንግስትን የልማትና የለውጥ ግቦች አቅጣጫ የሚጠቁሙ መሆን ይገባቸዋል ሲሉም ነው የገለጹት።

በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ የአፈር ምርምርና የእጽዋት ሥነ ምግብ ተመራማሪ ፕሮፌሰር ሸለመ በየነ በበኩላቸው፣ በዩኒቨርሲቲው የሚካሄዱ የጥናትና ምርምር ሥራዎች ለሀገር እድገት ከፍተኛ ድርሻ እያበረከቱ መሆናቸውን አስታውሰዋል።
የምርምር ውጤቶቹ ልማትን በዘላቂነት ለማጠናከር ካላቸው ፋይዳ በተጨማሪ የአርሶ አደሩን ጊዜ፣ ጉልበትና ወጪን ለመቆጠብ እንዳስቻሉ ገልጸዋል።
በተለይም በአካባቢ ያሉ የልማት አቅሞች በአግባቡ ጥቅም ላይ የሚውሉበትን አማራጭ ማቅረብ ላይ ትኩረት መሰጠት እንዳለበት ነው የገለጹት።
ለምርምር ስራዎች ውጤታማነት ቅንጅታዊ አሰራርን መዘርጋትና ለዘርፉ የተመደበ በጀትን በአግባቡ ሥራ ላይ ማዋል እንደሚገባም ፕሮፌሰር ሸለመ አስገንዝበዋል።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026