ደቡብ ቤንች፤ግንቦት 24/2017 (ኢዜአ)፦በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በበልግ ዝናብና በመስኖ ከለማው የአትክልትና ስራስር ሰብሎች ከ18 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸውን ጨምሮ ሌሎች የስራ ኃላፊዎች በቤንች ሸኮ ዞን ደቡብ ቤንች ወረዳ በኩታ ገጠም እየለማ ያለውን የሽንኩርት ማሳ ተመልክተዋል።
አቶ ማስረሻ በላቸው በወቅቱ እንዳሉት፥ በክልሉ በበልግ ዝናብና በሁለተኛ ዙር መስኖ ከ100 ሺህ ሄክታር በላይ ማሳ ላይ የለማው የአትክልትና ስራስር ሰብል በጥሩ ሁኔታ ላይ ይገኛል።
ከለማው ማሳም ከ7 ሺህ ሄክታር በላዩ በሽንኩርት የተሸፈነ መሆኑን ተናግረዋል።
በአጠቃላይ በአትክልትና ስራስር ሰብል ከለማው ማሳ 18 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል ምርት እንደሚጠበቅ አመላክተዋል።
በተለይም በደቡብ ቤንች ወረዳ በአርሶ አደር ጓሮ የተጀመረው የሽንኩርት ልማት አሁን ላይ ተስፋፍቶ በኩታ ገጠም መመረት መቻሉ ከአካባቢው አልፎ ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ የሚያስችል እንደሆነም ተናግረዋል።
የቤንች ሸኮ ዞን ምክትል ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀብታሙ ካፍትን በበኩላቸው፥በዞኑ እየተከናወኑ ባሉ የግብርና ስራዎች ውጤት እየታየ ነው ብለዋል።
በደቡብ ቤንች ወረዳ የተጀመረውን የኩታ ገጠም ሽንኩርት ልማት በዞኑ ውስጥ ባሉ ሁሉም ወረዳዎች እንዲስፋፋ ጥረት እንደሚደረግ አመልክተዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025