
ደቡብ ቤንች፤ግንቦት 24/2017 (ኢዜአ)፦በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በበልግ ዝናብና በመስኖ ከለማው የአትክልትና ስራስር ሰብሎች ከ18 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸውን ጨምሮ ሌሎች የስራ ኃላፊዎች በቤንች ሸኮ ዞን ደቡብ ቤንች ወረዳ በኩታ ገጠም እየለማ ያለውን የሽንኩርት ማሳ ተመልክተዋል።
አቶ ማስረሻ በላቸው በወቅቱ እንዳሉት፥ በክልሉ በበልግ ዝናብና በሁለተኛ ዙር መስኖ ከ100 ሺህ ሄክታር በላይ ማሳ ላይ የለማው የአትክልትና ስራስር ሰብል በጥሩ ሁኔታ ላይ ይገኛል።
ከለማው ማሳም ከ7 ሺህ ሄክታር በላዩ በሽንኩርት የተሸፈነ መሆኑን ተናግረዋል።
በአጠቃላይ በአትክልትና ስራስር ሰብል ከለማው ማሳ 18 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል ምርት እንደሚጠበቅ አመላክተዋል።
በተለይም በደቡብ ቤንች ወረዳ በአርሶ አደር ጓሮ የተጀመረው የሽንኩርት ልማት አሁን ላይ ተስፋፍቶ በኩታ ገጠም መመረት መቻሉ ከአካባቢው አልፎ ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ የሚያስችል እንደሆነም ተናግረዋል።
የቤንች ሸኮ ዞን ምክትል ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀብታሙ ካፍትን በበኩላቸው፥በዞኑ እየተከናወኑ ባሉ የግብርና ስራዎች ውጤት እየታየ ነው ብለዋል።
በደቡብ ቤንች ወረዳ የተጀመረውን የኩታ ገጠም ሽንኩርት ልማት በዞኑ ውስጥ ባሉ ሁሉም ወረዳዎች እንዲስፋፋ ጥረት እንደሚደረግ አመልክተዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026