የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በክልሉ ለተጀመረው የልማትና የብልጽግና ጉዞ ስኬታማነት የንግዱ ማህበረሰብ ተሳትፎ ሊጠናከር ይገባል

Jun 3, 2025

IDOPRESS

ጋምቤላ፤ ግንቦት 25/2017(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል ለተጀመረው የልማትና የብልጽግና ጉዞ ስኬታማነት የንግዱ ማህበረሰብ ሁለንተናዊ ተሳትፎ ሊጠናከር እንደሚገባ ተመለከተ።

’’ለሁለንተናዊ ብልጽግና፣ የንግዱ ማህበረሰብ ሚና’’ በሚል መሪ ሃሳብ የንግዱ ማህበረሰብ የተሳተፈበት ውይይት ዛሬ በጋምቤላ ከተማ ተካሂዷል።

በብልጽግና ፓርቲ የጋምቤላ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አሽኔ አስቲን እንዳሉት መንግስት የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራ ይገኛል።

በክልሉ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የህዝቡን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተከናወኑ ስራዎች በርካታ ስኬቶች ተመዝግበዋል ብለዋል።

ይሁን እንጂ እየጨመረ የመጣውን የማህበረሰቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ፈላጎትና ጥያቄ ከመመለስ አኳያ ቀሪ ስራዎች መኖራቸውን አመልክተዋል።

መንግስት እየሰፋ የመጣውን የህዝቡን የልማት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ለሚያደርጋቸው ጥረቶች ስኬታማነት የንግዱ ማህበረሰብ ሁለንተናዊ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።

የንግዱ ማህበረሰብ በተለይም በኢንቨስትመንት ዘርፍ በመሰማራት ኢኮኖሚውን በመደገፍ በኩል ያለውን ድርሻ ሊያጠናክር እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

የውይይት መድረኩ ዓላማ የንግዱ ማህበረሰብ እየተከናወኑ ባሉት የልማት ስራዎች ዙሪያ የጠራ ግንዛቤ በመያዝ የልማት አጋርነቱን እንዲያጠናከር ለማስቻል መሆኑን አስታውቀዋል።

የክልሉ ንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ ምክልት ኃላፊ ኢንጂነር ኡሌሮ ኦፒዮው በበኩላቸው የንግዱ ማህበረሰብ የተረጋጋ የገበያ ስርዓት እንዲረጋገጥ ማድረግን ጨምሮ ለልማትና እድገት ሚናውን በበለጠ ሊወጣ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

ከመድረኩ ተሳተፊዎች መካከል አቶ ዋንግ ኩላንግ በሰጡት አስተያየት መንግስት ህዝቡን የልማት ተጠቃሚ ለማድረግ እያደረገ ያለው ጥረት የሚበረታታ ነው ብለዋል።

በመንግስት የተጀመሩ የልማት ስራዎችን ለማገዝ ዝግጁ መሆናቸውንም ጨምረው አመልክተዋል።

የንግዱ ማህበረሰብ መንግስት ለጀመራቸው የልማት ስራዎች ሚናውን ይወጣል ያሉት ደግሞ ሌላው የመድረኩ ተሳታፊ አቶ ፍቃዱ ቀናው ናቸው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.