ጋምቤላ፤ ግንቦት 25/2017(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል ለተጀመረው የልማትና የብልጽግና ጉዞ ስኬታማነት የንግዱ ማህበረሰብ ሁለንተናዊ ተሳትፎ ሊጠናከር እንደሚገባ ተመለከተ።
’’ለሁለንተናዊ ብልጽግና፣ የንግዱ ማህበረሰብ ሚና’’ በሚል መሪ ሃሳብ የንግዱ ማህበረሰብ የተሳተፈበት ውይይት ዛሬ በጋምቤላ ከተማ ተካሂዷል።
በብልጽግና ፓርቲ የጋምቤላ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አሽኔ አስቲን እንዳሉት መንግስት የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራ ይገኛል።
በክልሉ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የህዝቡን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተከናወኑ ስራዎች በርካታ ስኬቶች ተመዝግበዋል ብለዋል።
ይሁን እንጂ እየጨመረ የመጣውን የማህበረሰቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ፈላጎትና ጥያቄ ከመመለስ አኳያ ቀሪ ስራዎች መኖራቸውን አመልክተዋል።
መንግስት እየሰፋ የመጣውን የህዝቡን የልማት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ለሚያደርጋቸው ጥረቶች ስኬታማነት የንግዱ ማህበረሰብ ሁለንተናዊ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።
የንግዱ ማህበረሰብ በተለይም በኢንቨስትመንት ዘርፍ በመሰማራት ኢኮኖሚውን በመደገፍ በኩል ያለውን ድርሻ ሊያጠናክር እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
የውይይት መድረኩ ዓላማ የንግዱ ማህበረሰብ እየተከናወኑ ባሉት የልማት ስራዎች ዙሪያ የጠራ ግንዛቤ በመያዝ የልማት አጋርነቱን እንዲያጠናከር ለማስቻል መሆኑን አስታውቀዋል።
የክልሉ ንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ ምክልት ኃላፊ ኢንጂነር ኡሌሮ ኦፒዮው በበኩላቸው የንግዱ ማህበረሰብ የተረጋጋ የገበያ ስርዓት እንዲረጋገጥ ማድረግን ጨምሮ ለልማትና እድገት ሚናውን በበለጠ ሊወጣ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
ከመድረኩ ተሳተፊዎች መካከል አቶ ዋንግ ኩላንግ በሰጡት አስተያየት መንግስት ህዝቡን የልማት ተጠቃሚ ለማድረግ እያደረገ ያለው ጥረት የሚበረታታ ነው ብለዋል።
በመንግስት የተጀመሩ የልማት ስራዎችን ለማገዝ ዝግጁ መሆናቸውንም ጨምረው አመልክተዋል።
የንግዱ ማህበረሰብ መንግስት ለጀመራቸው የልማት ስራዎች ሚናውን ይወጣል ያሉት ደግሞ ሌላው የመድረኩ ተሳታፊ አቶ ፍቃዱ ቀናው ናቸው።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025