
ጋምቤላ፤ ግንቦት 25/2017(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል ለተጀመረው የልማትና የብልጽግና ጉዞ ስኬታማነት የንግዱ ማህበረሰብ ሁለንተናዊ ተሳትፎ ሊጠናከር እንደሚገባ ተመለከተ።
’’ለሁለንተናዊ ብልጽግና፣ የንግዱ ማህበረሰብ ሚና’’ በሚል መሪ ሃሳብ የንግዱ ማህበረሰብ የተሳተፈበት ውይይት ዛሬ በጋምቤላ ከተማ ተካሂዷል።
በብልጽግና ፓርቲ የጋምቤላ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አሽኔ አስቲን እንዳሉት መንግስት የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራ ይገኛል።
በክልሉ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የህዝቡን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተከናወኑ ስራዎች በርካታ ስኬቶች ተመዝግበዋል ብለዋል።
ይሁን እንጂ እየጨመረ የመጣውን የማህበረሰቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ፈላጎትና ጥያቄ ከመመለስ አኳያ ቀሪ ስራዎች መኖራቸውን አመልክተዋል።
መንግስት እየሰፋ የመጣውን የህዝቡን የልማት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ለሚያደርጋቸው ጥረቶች ስኬታማነት የንግዱ ማህበረሰብ ሁለንተናዊ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።
የንግዱ ማህበረሰብ በተለይም በኢንቨስትመንት ዘርፍ በመሰማራት ኢኮኖሚውን በመደገፍ በኩል ያለውን ድርሻ ሊያጠናክር እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
የውይይት መድረኩ ዓላማ የንግዱ ማህበረሰብ እየተከናወኑ ባሉት የልማት ስራዎች ዙሪያ የጠራ ግንዛቤ በመያዝ የልማት አጋርነቱን እንዲያጠናከር ለማስቻል መሆኑን አስታውቀዋል።
የክልሉ ንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ ምክልት ኃላፊ ኢንጂነር ኡሌሮ ኦፒዮው በበኩላቸው የንግዱ ማህበረሰብ የተረጋጋ የገበያ ስርዓት እንዲረጋገጥ ማድረግን ጨምሮ ለልማትና እድገት ሚናውን በበለጠ ሊወጣ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
ከመድረኩ ተሳተፊዎች መካከል አቶ ዋንግ ኩላንግ በሰጡት አስተያየት መንግስት ህዝቡን የልማት ተጠቃሚ ለማድረግ እያደረገ ያለው ጥረት የሚበረታታ ነው ብለዋል።
በመንግስት የተጀመሩ የልማት ስራዎችን ለማገዝ ዝግጁ መሆናቸውንም ጨምረው አመልክተዋል።
የንግዱ ማህበረሰብ መንግስት ለጀመራቸው የልማት ስራዎች ሚናውን ይወጣል ያሉት ደግሞ ሌላው የመድረኩ ተሳታፊ አቶ ፍቃዱ ቀናው ናቸው።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026