
ጋምቤላ፤ ግንቦት 25/2017(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል ለተጀመረው የልማትና የብልጽግና ጉዞ ስኬታማነት የንግዱ ማህበረሰብ ሁለንተናዊ ተሳትፎ ሊጠናከር እንደሚገባ ተመለከተ።
’’ለሁለንተናዊ ብልጽግና፣ የንግዱ ማህበረሰብ ሚና’’ በሚል መሪ ሃሳብ የንግዱ ማህበረሰብ የተሳተፈበት ውይይት ዛሬ በጋምቤላ ከተማ ተካሂዷል።
በብልጽግና ፓርቲ የጋምቤላ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አሽኔ አስቲን እንዳሉት መንግስት የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራ ይገኛል።
በክልሉ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የህዝቡን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተከናወኑ ስራዎች በርካታ ስኬቶች ተመዝግበዋል ብለዋል።
ይሁን እንጂ እየጨመረ የመጣውን የማህበረሰቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ፈላጎትና ጥያቄ ከመመለስ አኳያ ቀሪ ስራዎች መኖራቸውን አመልክተዋል።
መንግስት እየሰፋ የመጣውን የህዝቡን የልማት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ለሚያደርጋቸው ጥረቶች ስኬታማነት የንግዱ ማህበረሰብ ሁለንተናዊ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።
የንግዱ ማህበረሰብ በተለይም በኢንቨስትመንት ዘርፍ በመሰማራት ኢኮኖሚውን በመደገፍ በኩል ያለውን ድርሻ ሊያጠናክር እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
የውይይት መድረኩ ዓላማ የንግዱ ማህበረሰብ እየተከናወኑ ባሉት የልማት ስራዎች ዙሪያ የጠራ ግንዛቤ በመያዝ የልማት አጋርነቱን እንዲያጠናከር ለማስቻል መሆኑን አስታውቀዋል።
የክልሉ ንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ ምክልት ኃላፊ ኢንጂነር ኡሌሮ ኦፒዮው በበኩላቸው የንግዱ ማህበረሰብ የተረጋጋ የገበያ ስርዓት እንዲረጋገጥ ማድረግን ጨምሮ ለልማትና እድገት ሚናውን በበለጠ ሊወጣ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
ከመድረኩ ተሳተፊዎች መካከል አቶ ዋንግ ኩላንግ በሰጡት አስተያየት መንግስት ህዝቡን የልማት ተጠቃሚ ለማድረግ እያደረገ ያለው ጥረት የሚበረታታ ነው ብለዋል።
በመንግስት የተጀመሩ የልማት ስራዎችን ለማገዝ ዝግጁ መሆናቸውንም ጨምረው አመልክተዋል።
የንግዱ ማህበረሰብ መንግስት ለጀመራቸው የልማት ስራዎች ሚናውን ይወጣል ያሉት ደግሞ ሌላው የመድረኩ ተሳታፊ አቶ ፍቃዱ ቀናው ናቸው።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026