የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በክልሉ የግብርና ግብዓት አጠቃቀም ላይ የታየው መሻሻል ሊጠናከር ይገባል

Jun 4, 2025

IDOPRESS

ሠመራ፣ግንቦት 26/2017(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል የግብርና ግብዓት አጠቃቀም ላይ የታየው መሻሻል መጠናከር እንዳለበት ተመላከተ።

ግብርና ሚኒስቴር በአፋር ክልል የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት፣ አጠቃቀምና ስርጭት ላይ ከክልሉ ባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ መክሯል።

በመድረኩ የተገኙት በግብርና ሚኒስቴር የግብርና ግብዓት አቅርቦት መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ መንግስቱ ተስፋ እንዳሉት፥ መንግስት የተለያዩ የግብርና ግብዓቶችን በማቅረብ ምርታማነትን ለማሳደግ እየሠራ ነው።

በዚህም በአፋር ክልል በ2016 ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት እንዲጀመር ማስቻሉን ገልጸው፤ አፈፃፀሙም የሚበረታታ መሆኑን ተናግረዋል።

በክልሉ የግብርና ግብዓት አጠቃቀም መሻሻል እየታየ መሆኑን አንስተው፥ ተግባሩ ሊጠናከር እንደሚገባም አመልክተዋል።

መድረኩ የተዘጋጀውም በክልሉ የተሳለጠ የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦትና የግብርና ግብዓት አጠቃቀምን በተመለከተ ለባለድርሻ አካላት ግንዛቤ ለመፍጠር መሆኑንም ጠቁመዋል።

የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ሐሩን ዓሊ በበኩላቸው፥ የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት በቅርቡ የተጀመረ ቢሆንም በግብዓትነት መጠቀም ላይ ተስፋ ሰጪ አተገባበር ታይቷል ብለዋል።

በበጀት ዓመቱ በክልሉ በሚገኙ ሰባት ወረዳዎች የአፈር ማዳበሪያ በማቅረብ ላይ እንደሚገኙ የገለፁት ደግሞ በክልሉ የደንከሊያ ግብርና ግብዓት አቅርቦት ህብረት ስራ ዩኒየን ስራ አስኪያጅ አቶ መሰለ ይማም ናቸው።

ለአራት መሠረታዊ ማህበራትና ለኢንቨስተሮች ዩሪያና ዳፕ ማዳበሪያዎችን በማቅረብ ላይ መሆናቸውን ገልፀው፥ እስካሁን 25 ሺህ 995 ኩንታል ማዳበሪያ ማከፋፈላቸውን ገልፀዋል።

የጋሊ ኮማ ሁለገብ የገበሬዎች ህብረት ስራ ዩኒየን ስራ አስኪያጅ ወጣት ሰኢድ ሲራጅ በበኩሉ፥ 1 ሺህ 4 ኩንታል ማዳበሪያ ስርጭት ማከናወኑን ተናግሯል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.