አዲስ አበባ፤ግንቦት 26/2017(ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የተገኙ ውጤቶች የኢትዮጵያን ማንሰራራት ማሳያዎች መካከል መሆናቸውን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ያሉት በአማራ ክልል በጎንደር ከተማ በተካሄደው የ3ኛው “የኢትዮጵያ ታምርት እኛም እንሸምት” ንቅናቄ አካል የሆነ ኤክስፖ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ነው።
በንግግራቸው ጎንደር የትናንት፣ የዛሬና የነገ ሥልጣኔ መገናኛ ከመሆኗም በላይ የአምራች ኢንዱስትሪ ኮሪደር እየሆነች መምጣቷን አንስተዋል።
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የማንሰራራት ጉዟችን አንዱ ምልክት ነው ብለዋል።
በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የተገኙ ውጤቶች የኢትዮጵያን ማንሰራራት ማሳያዎች መካከል መሆናቸውን የገለጹት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ኢትዮጵያ በብዙ የምታመርት በትንሹ ደግሞ የምትሸምት ሀገር እንድትሆን እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።
የአማራ ክልል በችግር ጊዜም ቢሆን ሰላምን እያሰፈነ የልማት አርበኛ ሆኖ መቀጠል የመቻሉ ህያው ምስክር መሆኑንም ጠቅሰዋል።
በተሳሳተ መንገድ ወደጫካ ታጥቀው የገቡ ልጆቿ የመንግሥትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው እየመጡ ወደ ማህበረሰባቸው እየተቀላቀሉ ይገኛሉ ብለዋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ጎንደር እንደ አዲስ እየተወለደች፣ እንደ አዲስ እየተሠራች እንዲሁም እየፈካች መሆኑንም ጠቅሰው፤ ዛሬ በከተማዋ በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍም የተመለከቱት ተግባራትም ይሄንኑ የሚያረጋግጡ መሆናቸውን ገልጸዋል።
መንግሥት ለሰላም እንዲሁም አምራች ኢንዱስትሪውን ጨምሮ ለልማት የሰጠውን ትኩረት አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025