
አዲስ አበባ፤ግንቦት 26/2017(ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የተገኙ ውጤቶች የኢትዮጵያን ማንሰራራት ማሳያዎች መካከል መሆናቸውን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ያሉት በአማራ ክልል በጎንደር ከተማ በተካሄደው የ3ኛው “የኢትዮጵያ ታምርት እኛም እንሸምት” ንቅናቄ አካል የሆነ ኤክስፖ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ነው።

በንግግራቸው ጎንደር የትናንት፣ የዛሬና የነገ ሥልጣኔ መገናኛ ከመሆኗም በላይ የአምራች ኢንዱስትሪ ኮሪደር እየሆነች መምጣቷን አንስተዋል።
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የማንሰራራት ጉዟችን አንዱ ምልክት ነው ብለዋል።
በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የተገኙ ውጤቶች የኢትዮጵያን ማንሰራራት ማሳያዎች መካከል መሆናቸውን የገለጹት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ኢትዮጵያ በብዙ የምታመርት በትንሹ ደግሞ የምትሸምት ሀገር እንድትሆን እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።
የአማራ ክልል በችግር ጊዜም ቢሆን ሰላምን እያሰፈነ የልማት አርበኛ ሆኖ መቀጠል የመቻሉ ህያው ምስክር መሆኑንም ጠቅሰዋል።

በተሳሳተ መንገድ ወደጫካ ታጥቀው የገቡ ልጆቿ የመንግሥትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው እየመጡ ወደ ማህበረሰባቸው እየተቀላቀሉ ይገኛሉ ብለዋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ጎንደር እንደ አዲስ እየተወለደች፣ እንደ አዲስ እየተሠራች እንዲሁም እየፈካች መሆኑንም ጠቅሰው፤ ዛሬ በከተማዋ በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍም የተመለከቱት ተግባራትም ይሄንኑ የሚያረጋግጡ መሆናቸውን ገልጸዋል።
መንግሥት ለሰላም እንዲሁም አምራች ኢንዱስትሪውን ጨምሮ ለልማት የሰጠውን ትኩረት አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026