ቦንጋ፤ግንቦት 27/2017 (ኢዜአ)፡-ለተረጋጋ ፖለቲካዊ፣ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሥርዓት ግንባታ የንግዱ ማኅበረሰብ ሚና ወሳኝ ነው ሲሉ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ተናገሩ።
"የብልጽግና ጉዟችንና የንግዱ ማኅበረሰብ ሚና" በሚል መሪ ሀሳብ ክልላዊ የንግዱ ማኅበረሰብ የውይይት መድረክ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ነው።
በመድረኩ ላይ ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) እንዳሉት፥ ለተረጋጋ ፖለቲካዊ፣ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሥርዓት ግንባታ የንግዱ ማኅበረሰብ ሚና ወሳኝ ነው።
በተለይ ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገት እንዲመዘገብ ኢንቨስትመንት፣ ኢንዱስትሪ፣የሥራ ዕድል ፈጠራና ማኅበራዊ አገልግሎትን ማጠናር እንደሚገባ ገልጸው፣ለዚህም የንግዱ ማህበረሰብ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።
መንግስት የንግዱን ሥርዓት ለማሳለጥና ነጋዴውን ለማበረታታት የተለያዩ ማዕቀፎችን መተግበሩን አጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም ኢንጂነር ነጋሽ (ዶ/ር) ገልጸዋል።
የንግዱ ማህበረሰብም ይህን ዕድል በመጠቀም ቀጣይነት ያለው የኢኮኖሚ ዕድገት እንዲመዘገብና የተረጋጋ የገበያ ሥርዓት እንዲኖር ሚናውን እንዲወጣም ጠይቀዋል።
መንግስት ጤናማ የንግድ ሥርአትን በመፍጠር ገበያን ለማረጋጋት የሚያደርገውን ጥረት ማገዝ እንዳለበትም አስገንዝበዋል።
የውይይቱ ተሳታፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የንግድ ሥራና የልማት እንቅስቃሴዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025