
ቦንጋ፤ግንቦት 27/2017 (ኢዜአ)፡-ለተረጋጋ ፖለቲካዊ፣ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሥርዓት ግንባታ የንግዱ ማኅበረሰብ ሚና ወሳኝ ነው ሲሉ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ተናገሩ።
"የብልጽግና ጉዟችንና የንግዱ ማኅበረሰብ ሚና" በሚል መሪ ሀሳብ ክልላዊ የንግዱ ማኅበረሰብ የውይይት መድረክ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ነው።

በመድረኩ ላይ ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) እንዳሉት፥ ለተረጋጋ ፖለቲካዊ፣ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሥርዓት ግንባታ የንግዱ ማኅበረሰብ ሚና ወሳኝ ነው።
በተለይ ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገት እንዲመዘገብ ኢንቨስትመንት፣ ኢንዱስትሪ፣የሥራ ዕድል ፈጠራና ማኅበራዊ አገልግሎትን ማጠናር እንደሚገባ ገልጸው፣ለዚህም የንግዱ ማህበረሰብ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።
መንግስት የንግዱን ሥርዓት ለማሳለጥና ነጋዴውን ለማበረታታት የተለያዩ ማዕቀፎችን መተግበሩን አጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም ኢንጂነር ነጋሽ (ዶ/ር) ገልጸዋል።
የንግዱ ማህበረሰብም ይህን ዕድል በመጠቀም ቀጣይነት ያለው የኢኮኖሚ ዕድገት እንዲመዘገብና የተረጋጋ የገበያ ሥርዓት እንዲኖር ሚናውን እንዲወጣም ጠይቀዋል።
መንግስት ጤናማ የንግድ ሥርአትን በመፍጠር ገበያን ለማረጋጋት የሚያደርገውን ጥረት ማገዝ እንዳለበትም አስገንዝበዋል።
የውይይቱ ተሳታፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የንግድ ሥራና የልማት እንቅስቃሴዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026