
አዲስ አበባ፤ግንቦት 28/2017(ኢዜአ)፦አዲስ አበባ ከተማ የነዋሪዎቿን ህይወት በማሻሻል ረገድ እያስመዘገበች ለምትገኘው ለውጥ የከተማ ግብርና ቁልፍ ምሰሶ መሆኑን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።
ዛሬ ማምሻውን ከንቲባ አዳነች ከስሎቪንያ ፕሬዝዳንት ናታሳ ፒርክ ሙሳር (ዶ/ር) እና ልዑካቸው ጋር በመሆን ዘመናዊ የንብ ማነብ ሰርቶ ማሳያ ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር አካሒደዋል።
በመርሃ-ግብሩ ላይ ከንቲባ አዳነች አቤቤ እንደገለጹት፥ የንብ ማነብና ከተማ ግብርና ስራ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥና አካባቢን ለመጠበቅ ጠቀሜታ እንዳለው ተናግረዋል።
ብዝሃ ህይወትን ለመጠበቅና የምግብ ሉዓላዊነት የማረጋገጥ ስራ ከአየር ንብረት ለውጥ ስትራቴጂ ጋር የተሰናሰለ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
አዲስ አበባ የጋራ የልማት ግብ ካላቸው ጋር በትብብር እንደምትሰራም ገልጸዋል።
በአዲስ ዙ ፓርክ በይፋ የተጀመረው ዘመናዊ የንብ ማነብ ሰርቶ ማሳያ የአለም አቀፍ ትብብር ማሳያ ጭምር መሆኑን ጠቅሰው፤ ለትምህርትና ለቱሪስት ዘርፍም ጠቃሚ ነው ብለዋል።

የስሎቪንያ ፕሬዝዳንት ናታሳ ፒርክ ሙሳር (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ ሃገራቸው በኢትዮጵያ ዘመናዊ የንብ ማነብ ስራን ለማጠናከር የባለሙያና ቴክኖሎጂ ድጋፍ እንደምታደርግ ገልጸዋል።
አገሪቱ በዘመናዊ ንብ ማነብ ላይ ያላትን ልምድ ለኢትዮጵያ በማጋራት ከዘርፉ የበለጠ ተጠቃሚ ለማድረግ ትሰራለችም ብለዋል።
ስሎቪንያና ኢትዮጵያ መልካም የዲፕሎማሲ ግንኙነት ያላቸው አገራት ናቸው ያሉት ፕሬዝዳንቷ የሀገራቱ ግንኙነት በሌሎች የትብብር መስኮችም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026