የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የነዋሪዎችን ህይወት ማሻሻል ላይ በማተኮር ለተከናወነው ስኬታማ ስራ የከተማ ግብርና ቁልፍ ሚና አለው- ከንቲባ አዳነች አቤቤ

Jun 6, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ግንቦት 28/2017(ኢዜአ)፦አዲስ አበባ ከተማ የነዋሪዎቿን ህይወት በማሻሻል ረገድ እያስመዘገበች ለምትገኘው ለውጥ የከተማ ግብርና ቁልፍ ምሰሶ መሆኑን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።


ዛሬ ማምሻውን ከንቲባ አዳነች ከስሎቪንያ ፕሬዝዳንት ናታሳ ፒርክ ሙሳር (ዶ/ር) እና ልዑካቸው ጋር በመሆን ዘመናዊ የንብ ማነብ ሰርቶ ማሳያ ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር አካሒደዋል።


በመርሃ-ግብሩ ላይ ከንቲባ አዳነች አቤቤ እንደገለጹት፥ የንብ ማነብና ከተማ ግብርና ስራ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥና አካባቢን ለመጠበቅ ጠቀሜታ እንዳለው ተናግረዋል።


ብዝሃ ህይወትን ለመጠበቅና የምግብ ሉዓላዊነት የማረጋገጥ ስራ ከአየር ንብረት ለውጥ ስትራቴጂ ጋር የተሰናሰለ መሆኑንም ጠቅሰዋል።


አዲስ አበባ የጋራ የልማት ግብ ካላቸው ጋር በትብብር እንደምትሰራም ገልጸዋል።


በአዲስ ዙ ፓርክ በይፋ የተጀመረው ዘመናዊ የንብ ማነብ ሰርቶ ማሳያ የአለም አቀፍ ትብብር ማሳያ ጭምር መሆኑን ጠቅሰው፤ ለትምህርትና ለቱሪስት ዘርፍም ጠቃሚ ነው ብለዋል።


የስሎቪንያ ፕሬዝዳንት ናታሳ ፒርክ ሙሳር (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ ሃገራቸው በኢትዮጵያ ዘመናዊ የንብ ማነብ ስራን ለማጠናከር የባለሙያና ቴክኖሎጂ ድጋፍ እንደምታደርግ ገልጸዋል።


አገሪቱ በዘመናዊ ንብ ማነብ ላይ ያላትን ልምድ ለኢትዮጵያ በማጋራት ከዘርፉ የበለጠ ተጠቃሚ ለማድረግ ትሰራለችም ብለዋል።


ስሎቪንያና ኢትዮጵያ መልካም የዲፕሎማሲ ግንኙነት ያላቸው አገራት ናቸው ያሉት ፕሬዝዳንቷ የሀገራቱ ግንኙነት በሌሎች የትብብር መስኮችም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.