ባህርዳር፤ግንቦት 30/2017(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል አርሶ አደሮች በዓመት እስከ ሶስት ጊዜ በመስኖ በማልማት እያገኙት ያለው ምርት ከፍጆታቸው አልፎ በመሸጥ ሀብት እንዲያፈሩ እያገዛቸው መሆኑ ተገለጸ።
በክልሉ በዘንድሮ የበጋ ወቅት በመጀመሪያው ዙር መስኖ ከለማው ማሳ ከ30 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታውቋል።
ከተሰበሰበው ውስጥም ሰባት ነጥብ አንድ ሚሊዮን ኩንታሉ የስንዴ ምርት መሆኑ ተመልክቷል።
አርሶ አደር ሃብቴ አበራ በአዊ ዞን የጓጉሳ ወረዳ ነዋሪ ሲሆኑ፤ ቀደም ሲል ጀምሮ በበጋ መስኖ ልማት ላይ በመሳተፍ ያገኙትን ምርት ከፍጆታቸው የተረፈውን በመሸጥ በከተማ መኖሪያ ቤት ገንብተው ቋሚ ሃብት ማፍራታቸውን ለኢዜአ ተናግረዋል።
ያገኙትን ጥቅም በማስፋትም ዘንድሮ ሁለት ሄክታር የሚጠጋ መሬት በስንዴ፣ሽንኩርት፣ድንችና ቀይ ስር በማልማት 162 ኩንታል ምርት ማግኘታቸውን ገልጸዋል።
በዞኑ የጓንጓ ወረዳ አርሶ አደር አርሶ አደር ጥላሁን ካሳሁን በበኩላቸው፤ ያላቸውን ከሩብ ሄክታር በላይ መሬት በመስኖ ሽንኩርት አልምተው ያገኙትን 20 ኩንታል ምርት ለመሸጥ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።
አሁን ላይ የሽንኩርት ምርት ዋጋ ጥሩ በመሆኑ ሰሞኑን የሰበሰቡትን ምርት በተሻለ ዋጋ ሸጠው ተጠቃሚ ለመሆን እየሰሩ መሆኑን አስረድተዋል።
የምናከናውነው የበጋ መስኖ ልማት የምግብ ፍጆታችንን አሟልተን ተጨማሪ ሃብትና ጥሪት እንድናፈራ ረድቶናል ያሉት ደግሞ በደቡብ ጎንደር ዞን የደራ ወረዳ አርሶ አደር አዳሙ ሞላ ናቸው።
በየዓመቱ ሽንኩርት፣ ቲማቲም፣ ጥቅል ጎመንና የበቆሎ ሰብል በማልማት የሚያገኙት ምርት ከፍጆታቸው አልፎ ለገበያው አቅርበው በመሸጥ ሀብት እንዲያፈሩ እያገዛቸው መሆኑን ገልጸዋል።
በዘንድሮው በጋም በአንድ ሄክታር ተኩል መሬት ሽንኩርት፣ ቲማቲምና ስንዴ በማልማት 93 ኩንታል ምርት ማግኘታቸውን ጠቁመው፥ከዚህ ውስጥ 70 ኩንታሉን በተሻለ ዋጋ መሸጣቸውን አስታውቀዋል።
በክልሉ ግብርና ቢሮ የመስኖና ሆልቲ ካልቸር ልማት ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክተር አቶ ይበልጣል ወንድምነው፤ በክልሉ በመጀመሪያው ዙር መስኖ 330 ሺህ 900 ሄክታር መሬት መልማቱን ተናግረዋል።
አንድ ነጥብ ሁለት ሚሊዮን አርሶ አደሮች በማሳተፍ በተካሄደው የመስኖ ልማት 47 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እስካሁን 30 ነጥብ አንድ ሚሊዮን ኩንታል ምርት መሰብሰቡን ገልጸዋል።
ከተሰበሰበው ምርት ውስጥም ሰባት ነጥብ አንድ ሚሊዮን ኩንታሉ የስንዴ ምርት መሆኑን አመልክተዋል።
በሁለተኛ ዙር መስኖ ልማት ደግሞ በተለያየ አትክልትና ሰብል እየለማ ካለው 113 ሺህ ሄክታር መሬት 15 ሚሊዮን ኩንታል እንደሚጠበቅ ጠቁመዋል።
ከክልሉ ግብርና ቢሮው የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው፥ባለፈው ዓመት የበጋ ወቅት በክልሉ በሁለት ዙሮች በመስኖ ከለማው 299 ሺህ ሄክታር ማሳ ላይ 43 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ተገኝቷል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025