የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የፕሮጀክቶች ግንባታን በጥራትና በፍጥነት ከማጠናቀቅ አኳያ አመርቂ ውጤቶች ተመዝግበዋል - ሚኒስትር አህመድ ሽዴ 

Jun 9, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የፕሮጀክቶች ግንባታን በጥራትና በፍጥነት ከማጠናቀቅ አኳያ አመርቂ ውጤቶች መመዝገባቸውን የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ገለጹ፡፡

የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ የተሟላ ማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ አፈጻጸምና በሌሎች ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ዙሪያ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በማብራሪያቸውም ባለፉት የለውጥ ዓመታት የመንግስት የፕሮጀክቶች አፈጻጸም በፍጥነትና በጥራት በከፍተኛ ደረጃ ማደጉን ተናግረዋል፡፡

በዚህም በመንገድ ፕሮጀክቶች አፈጻጸም አመርቂ ስራዎች መከናወናቸውን ጠቁመው፤ በአሁኑ ወቅት ከ22ሺህ ኪሎ ሜትር በላይ የመንገድ ፕሮጀክቶች በግንባታ ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

በመስኖ ልማት ረገድም የተሻለ አፈጻጸም መመዝገቡን ሚኒስትሩ አንስተው፤ የተጀመሩ ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የቱሪዝም መዳረሻ ልማቶችን በታለመላቸው ጊዜና ጥራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ በዚህም በርካቶቹ ተጠናቀው ወደ አገልግሎት መግባታቸውን ነው የገለጹት፡፡

በተጨማሪም ለማህበራዊ አገልግሎት የሚውሉ የልማት ፕሮጀክቶች አፈጻጸም አመርቂ መሆናቸውንም ጠቁመዋል፡፡

የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ የውጭ ምንዛሪ ተመን በገበያ መወሰን ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ከፖሊሲ ጋር የተገናኙ የኮንትሮባንድ ግፊቶች በከፍተኛ ሁኔታ መቀነሳቸውን ተናግረዋል፡፡

ማሻሻያውን ተከትሎም በወርቅ ግብይት ላይ የነበረው የኮንትሮባንድ ችግር መፈታቱን ነው የጠቀሱት፡፡

ኢትዮጵያ ከቀጣናው ሀገራት ጋር የምታደርገው የንግድ ግንኙነት፣ የመሠረተ ልማት ትስስርና የኢነርጂ አቅርቦት ተጠናክረው መቀጠላቸውንም አብራርተዋል፡፡

የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት በቀጣይ ዓመታት የሚኖረውን የማክሮ ኢኮኖሚ ትንበያ ማዕከል ያደረገ፣ የመንግስትን የገቢ አቅም በመተንበይ፣ የሚኖሩ ሌሎች ገቢዎችን ታሳቢ በማድረግና የመንግስትን የወጪ ፍላጎት በመተንተን የተዘጋጀ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

በጀቱ የተጀመሩ የልማት ስራዎችን ማስቀጠል፣ ማህበራዊ ድጎማዎችን እና የተረጋጋ የማክሮ ኢኮኖሚን ከማስቀጠልና ሌሎች ተግባራትን በውጤታማነት ከማከናወን አኳያ ትልቅ ፋይዳ ያለው መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በሁሉም አመላካቾች አመርቂ ውጤቶችን እያስመዘገበ መሆኑን ሚኒስትሩ መገልጻቸው ይታወቃል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.