የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በኦሮሚያ ክልል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ውጤታማ ነው

Jun 11, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2017(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ውጤታማ መሆኑን የክልሉ ምክትል ፕሬዚዳንት አወሉ አብዲ ገለጹ።


ምክትል ፕሬዚዳንቱ በክልሉ የበጀት አመቱ የልማት ፕሮጀክቶች አፈጻጸምን የተመለከተ መግለጫ ሰጥተዋል።


በመግለጫቸውም የክልሉ መንግስት በበጀት አመቱ አስተማማኝ ሰላም ከመገንባት ጎን ለጎን የመሠረተ ልማት ዝርጋታዎችን በስፋት አከናውኗል ብለዋል።


አስተማማኝ ሰላምን ከመገንባት አንጻር ህብረተሰቡን ባሳተፈ መልኩ በተሰራው ስራ ሰላምና ደህንነት ማረጋገጥ ተችሏል ነው ያሉት።


ለተገኘው ሰላም ህብረተሰቡ ትልቅ ምስጋና እንደሚገባው ጠቅሰው ሰላምን ለማጽናት የሚያግዙ ቀሪ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አመላክተዋል።


በተገኘው ሰላም ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ስራዎችን ቀጣይነት ባለው መልኩ ማከናወን እንደተቻለም ገልጸዋል።


የክልሉ መንግስት የመሠረተ ልማት ስራዎች ወጥነት ባለው መልኩ በጥራትና በፍጥነት እንዲከናወኑ በልዩ ትኩረት ሲሰራ መቆየቱንም ጠቅሰዋል።


በበጀት አመቱ የህብረተሰቡ የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ሆነው የቆዩ የመንገድ፣ የውሀ፣ የትምህርትና የጤና መሠረት ልማት ስራዎች በስፋት ተከናውነዋል ብለዋል።


በበጀት አመቱ ከ200 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ከ34ሺህ በላይ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች ሲከናወኑ መቆየታቸውን አመልክተዋል።


ከፕሮጀክቶቹ መካከል 73 በመቶ የሚሆኑት በህዝብ ተሳትፎ የተከናወኑና ቀሪዎቹ በመንግሥትና በአጋር አካላት የተከናወኑ መሆኑንም አንስተዋል።


አጠቃላይ በግንባታ ላይ ከሚገኙ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች መካካል 27ሺህ የሚሆኑት ግንባታቸው ተጠናቆ ለምረቃ መዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል።


በክልሉ በህዝብ ተሳትፎ ከተከናወኑ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች መካከል 11ሺህ የመምህራን መኖሪያ ቤቶች፣ 4ሺህ የቅድመ መደበኛ እና 800 የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እንደሚገኙበት ጠቅሰዋል።


በተጨማሪም የትምህርት ቤቶች ደረጃ ማሻሻል፣ የህጻናት ማቆያና የህጻናት መጫወቻ ስፍራዎች፣ እንዲሁም የመንገድ ጥገናና የድልድይ ግንባታ ስራዎች በህብረተሰቡ ተሳትፎ የተከናወኑ መሆኑን አመልክተዋል።


በአጠቃላይ የክልሉ መንግስት የጀመራቸው ሰላምን የማጽናት እና ልማትን የማፋጠን ስራዎች የበለጠ ይጠናከራሉ ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026