የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በከተማዋ የተገነቡ የምርት ግብይት ማዕከላት አምራቹንና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ነው -ከንቲባ አዳነች አቤቤ

Jun 11, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2017(ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ ከተማ የተገነቡ የምርት ግብይት ማዕከላት አምራቹንና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት የኑሮ ውድነቱን እና የዋጋ ንረትን በመቀነስ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።

በአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) የላፍቶ ቁጥር ሁለት ሁለገብ የገበያ ማዕከል ዛሬ መርቀው ስራ አስጀምረዋል።


ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ በከተማዋ በተለያዩ አካባቢዎች የተገነቡ የገበያ ማዕከላት አምራቹንና ሸማቹን እንደ ድልድይ በቀጥታ በማገናኘት የኑሮ ውድነቱን እና የዋጋ ንረትን በመቀነስ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑን ተናግረዋል።

በዚህም ዛሬ የተመረቀው የላፍቶ ቁጥር 2 የገበያ ማዕከልም አምራቹንና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት የኑሮ ውድነቱን እና የዋጋ ንረትን በመቀነስ የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።

እስካሁን በከተማው በርካታ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፋይዳ ያላቸው ፕሮጀክቶች ተገንብተው አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን ተናግረዋል።

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ ህብረተሰቡ ጥራታቸውን የጠበቁ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኝና የኑሮ ውድነቱን ለመቀነስ የገበያ መሰረተ ልማቶችን የማስፋት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

የላፍቶ ቁጥር ሁለት ሁለገብ የገበያ ማዕከል በ8 ነጥብ 8 ሄክታር መሬት ላይ የተገነባ ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.