የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የኢትዮጵያ ምጣኔ ሃብት በ2018 በጀት ዓመት 8 ነጥብ 9 በመቶ እድገት እንደሚያሳይ ይጠበቃል- የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ

Jun 11, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሰኔ 3/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ምጣኔ ሃብት በ2018 በጀት ዓመት 8 ነጥብ 9 በመቶ እድገት እንደሚያሳይ እንደሚጠበቅ የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ ተናገሩ።

የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት 1 ነጥብ 93 ትሪሊዮን ብር ሆኖ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቧል።

ምክር ቤቱ ዛሬ ባካሄደው 35ኛ መደበኛ ስብሰባ የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ ያቀረቡትን የፌዴራል መንግሥት የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ የበጀት መግለጫ አዳምጧል፡፡


በመግለጫቸው መንግስት ተግባራዊ ያደረገው የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ አፈጻጸም ስኬታማ ውጤት በማምጣቱና የግል ኢንቨስትመንት በመጨመሩ ተግባራዊነቱ በቀጣዮቹ ዓመታትም ተጠናክሮ ይቀጥላል ነው ያሉት።

በዚህም በማክሮ ኢኮኖሚ አፈጻጸም የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችን በተሟላ ሁኔታ ለማቃለልና የአገሪቷን ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት ዘላቂና ቀጣይነት በማረጋገጥ የብልጽግና ጉዞውን ስኬታማ ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

የመካከለኛ ዘመን የማክሮ ኢኮኖሚና ፊዚካል ማዕቀፍን በመከተል አጠቃላይ የፌዴራል መንግስት የ2018 ጠቅላላ ወጪ በጀት 1 ነጥብ 93 ትሪሊዮን ብር ሆኖ መዘጋጀቱን ተናግረዋል፡፡

ይህም በ2017 በጀት ዓመት የተጨማሪ በጀትን ጨምሮ ከጸደቀው የወጪ በጀት የ34 ነጥብ 4 በመቶ እድገት አለው ብለዋል።

ከወጪ በጀቱ ውስጥ 1 ነጥብ 2 ትሪሊዮን ብር ለመደበኛ ወጪ፣ 415 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ለካፒታል ወጪ፣ 315 ቢሊዮን ብር ለክልሎች ድጋፍና 14 ቢሊዮን ብር ለዘላቂ ልማት ግቦች የተመደበ መሆኑን አብራርተዋል።

ጠቅላላ ከተያዘው የካፒታል በጀት ውስጥ 74 ነጥብ 5 በመቶ ድርሻ ያላቸው ከፍተኛ ትኩረት ለተሰጣቸው ዘርፎች መመደባቸውን ገልጸዋል።

በ2018 በጀት ዓመት የመንግስትን ገቢ አሰባሰብ ለማሳደግ የብሔራዊ መካከለኛ ዘመን የገቢ ስትራቴጂን አጠናክሮ መቀጠል አስፈላጊ መሆኑን ጠቅሰው፤ አዳዲስ የታክስ ፖሊሲዎችን በስራ ላይ ለማዋል ይሰራል ነው ያሉት።

በገቢ በኩል በ2018 በጀት ዓመት የፌዴራል መንግስት ጠቅላላ ገቢ የውጭ እርዳታን ጨምሮ 1 ነጥብ 5 ትሪሊዮን ብር እንደሚሆን መገመቱን አመልክተዋል።

በሁለተኛው የአገር በቀል ምጣኔ ሃብት መርሃ ግብር የተቀመጡ ማሻሻያዎች በግብርና፣ በኢንዱስትሪና በአገልግሎት ዘርፎች ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያስችሉ መሆናቸውን ጠቁመው፤ ኢኮኖሚው በ2018 በጀት ዓመት የተሻለ እድገት እንደሚያሳይ ገልጸዋል።

በዚህም የኢትዮጵያ የምጣኔ ሃብት እድገት በ2018 በጀት አመት የ8 ነጥብ 9 በመቶ እድገት እንደሚያስመዘግብም ይጠበቃል ብለዋል።

የምክር ቤቱ አባላት በሰጡት አስተያየት፤ ለ2018 በጀት ዓመት የተዘጋጀው ረቂቅ በጀት የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ውጤታማ ለማድረግ መታየት አለበት ያሏቸውን ጉዳዮች አንስተዋል።

መንግስት አዳዲስ ፕሮጀክቶችን ከመጀመር ይልቅ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅ በሰጠው ትኩረት ላይ ለተነሳውና ለሌሎች ጥያቄዎች ሚኒስትሩ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በጀቱ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን በተሳካ ሁኔታ ተግባራዊ ለማድረግ ሚናው ከፍተኛ በመሆኑ ባለበጀት መስሪያ ቤቶች የተመደበላቸውን በጀት ለታለመለት አላማ ማዋል እንዳለባቸው ሚኒስትር አህመድ ሽዴ አሳስበዋል።

ምክር ቤቱ በረቂቅ በጀቱ ላይ የተሰጡ አስተያየቶችን በማከል በዝርዝር እንዲያየው ለፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ መርቶታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026