
አዲስ አበባ፤ሰኔ 4/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ ተጋላጭ የሆኑና በአነስተኛ ማሳ የሚያመርቱ አርሶና አርብቶ አደሮችን የፋይናንስ አቅም በማሳደግ ምርትና ምርታማነታቸው እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ገለፁ።
በአነስተኛ ማሳ የሚያመርቱ አርሶአደሮች የአየር ንብረት ለውጥ ተጋላጭነትና የፋይናንስ አቅርቦት ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው።
የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) በውይይቱ መክፈቻ፥ ኢትዮጵያ በ10 ዓመቱ መሪ የልማት ዕቅዷ ለግብርና ዘርፍ በሰጠችው ትኩረት ምርትና ምርታማነትን የበለጠ ማሳደግ መቻሏን አንስተዋል።
በዚህም ለረጅም ዓመታት ሀገራዊ የስንዴ ፍጆታን ሙሉ ለሙሉ በሀገር ውስጥ ምርት በመሸፈን ከውጭ የሚገባውን አስቀርተናል ነው ያሉት።
አካታችና የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም የሚያስችል የኢኮኖሚ ማሻሻያ መደረጉንም ገልፀዋል።
ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በየዓመቱ የምትተክላቸው ችግኞች ምርትና ምርታማነትን ከማሳደግ ባለፈ በምግብ ራስን ለመቻል የምታደርገውን ጥረት እያገዘ ነው ብለዋል።
በሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቭም የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥና የበርካታ ዜጎችን የአመጋገብ ሥርዓት በመቀየር ረገድ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ነው የገለፁት።
በአነስተኛ ማሳ የሚያመርቱ አርሶና አርብቶ አደሮች ለአየር ንብረት ለውጥ የበለጠ ተጋላጭ መሆናቸውን ያነሱት ሚኒስትሩ፥ ኢትዮጵያ ተፅዕኖውን ለመቋቋም አሰራር መዘርጋቷን ገልፀዋል።
የግብርናና ገጠር ልማት ፖሊሲው አነስተኛ ማሳ ያላቸው አርሶ አደሮች በቀላሉ የፋይናንስ ብድር አቅርቦት እንዲያገኙ ዕድል መስጠቱን አመልክተዋል።
በዚህም ለአየር ንብረት ለውጥ ተጋላጭ የሆኑ አርሶና አርብቶ አደሮች የፋይናንስና የኢንሹራንስ አቅማቸውን የበለጠ እንዲያጠናክሩ በማገዝ ምርትና ምርታማነታቸው እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ ነው ብለዋል።
የገጠር ልማትን ለማረጋገጥ፣የህዝቡን ኑሮ ለማሻሻል፣ የፋይናንስ አቅርቦትን ተደራሽነት የበለጠ ለማጠናከር የመረጃ አያያዝ ስርዓትን የማዘመን ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም ተናግረዋል።
አካታች የፋይናንስ ሥርዓት በመዘርጋት የገጠር ልማትን ለማረጋገጥ የባለድርሻ አካላት ትብብርና ቅንጅታዊ አሰራር የበለጠ ተጠናክሮ እንዲቀጥልም ጠይቀዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026