የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ክልሉ የአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ያለውን አቅም ለመጠቀም በጥናት ላይ የተመሰረተ ስራ ተከናውኗል - ቢሮው

Jun 12, 2025

IDOPRESS

ሀዋሳ፤ ሰኔ 4/2017(ኢዜአ)፦ የሲዳማ ክልል በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ያለውን አቅም መጠቀም የሚያስችል ስራ እያከናወነ መሆኑን የክልሉ ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ አስታወቀ።

ቢሮው ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በዘርፉ ላይ ባስጠናቸው የተለያዩ ጥናቶች ላይ ያተኮረ የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው።

የሲዳማ ክልል ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ጎሳዬ ጎዳና በዚህ ጊዜ እንደገለጹት ቢሮው በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ያለውን አቅም መጠቀም የሚያስችል በጥናት የተደገፈ ስራ እያከናወነ ነው።


ለዚህም ከ2014 ጀምሮ ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር የአምራች ኢንዱስትሪ ፍኖተ ካርታ ማዘጋጀቱን ገልጸዋል።

ፍኖተ ካርታውን ተግባራዊ ማድረግ የሚያስችል የ10 ዓመት ስትራቴጂክ እቅድና ይህን ተግባራዊ ለማድረግ አቅሞችን ለይቶ የሚሳይ ጥናት መደረጉን አስረድተዋል።

የዛሬው መድረክም ባለድርሻ አካላት ለጥናቶቹ ግብዓት የሚሆኑ ሀሳቦችን እንዲያነሱ የሚያግዝ ነው ብለዋል።

የጥናቱ ዋና ዓላማም አምራች ኢንዱስትሪው በስራ እድል ፈጠራ፣ ተኪ ምርቶችን በማምረት፣ የውጭ ምንዛሬን በማስገኘት፣ በቴክኖሎጂ ሽግግርና በሌሎች ወሳኝ ዘርፎች የሚያስገኘውን ዘርፈ ብዙ ፋይዳ ማሳደግ መሆኑንም አመልክተዋል።

በተለይም እንደክልል ያለውን ጠባብ መሬት በተገቢው በመጠቀም ወደ ኢንዱስትሪ ለመሸጋገር የሚደረገውን ጥረት እንደሚያግዝ ተናግረዋል።

በመድረኩ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞን ጨምሮ የክልል ቢሮ ኃላፊዎች የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ችሮታው አየለ(ዶ/ር) እና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ ነው-ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ

ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

May 21, 2026

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026