
ሀዋሳ፤ ሰኔ 4/2017(ኢዜአ)፦ የሲዳማ ክልል በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ያለውን አቅም መጠቀም የሚያስችል ስራ እያከናወነ መሆኑን የክልሉ ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ አስታወቀ።
ቢሮው ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በዘርፉ ላይ ባስጠናቸው የተለያዩ ጥናቶች ላይ ያተኮረ የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው።
የሲዳማ ክልል ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ጎሳዬ ጎዳና በዚህ ጊዜ እንደገለጹት ቢሮው በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ያለውን አቅም መጠቀም የሚያስችል በጥናት የተደገፈ ስራ እያከናወነ ነው።

ለዚህም ከ2014 ጀምሮ ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር የአምራች ኢንዱስትሪ ፍኖተ ካርታ ማዘጋጀቱን ገልጸዋል።
ፍኖተ ካርታውን ተግባራዊ ማድረግ የሚያስችል የ10 ዓመት ስትራቴጂክ እቅድና ይህን ተግባራዊ ለማድረግ አቅሞችን ለይቶ የሚሳይ ጥናት መደረጉን አስረድተዋል።
የዛሬው መድረክም ባለድርሻ አካላት ለጥናቶቹ ግብዓት የሚሆኑ ሀሳቦችን እንዲያነሱ የሚያግዝ ነው ብለዋል።
የጥናቱ ዋና ዓላማም አምራች ኢንዱስትሪው በስራ እድል ፈጠራ፣ ተኪ ምርቶችን በማምረት፣ የውጭ ምንዛሬን በማስገኘት፣ በቴክኖሎጂ ሽግግርና በሌሎች ወሳኝ ዘርፎች የሚያስገኘውን ዘርፈ ብዙ ፋይዳ ማሳደግ መሆኑንም አመልክተዋል።
በተለይም እንደክልል ያለውን ጠባብ መሬት በተገቢው በመጠቀም ወደ ኢንዱስትሪ ለመሸጋገር የሚደረገውን ጥረት እንደሚያግዝ ተናግረዋል።
በመድረኩ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞን ጨምሮ የክልል ቢሮ ኃላፊዎች የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ችሮታው አየለ(ዶ/ር) እና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026