የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በሲዳማ ክልል የአምራች ኢንዱስትሪውን አቅም በማሳደግ የክልሉን ህዝብ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ - ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

Jun 12, 2025

IDOPRESS

ሀዋሳ፤ ሰኔ 4/2017(ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የአምራች ኢንዱስትሪውን አቅም በማሳደግ የክልሉን ህዝብ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉየክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ገለጹ።

የክልሉ ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ከሀዋሳ ዪኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በኢንዱስትሪ ልማት ላይ ባስጠናቸው ጥናቶች ዙሪያ የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ ተካሂዷል።

የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ እንደገለጹት የአምራች ኢንዱስትሪውን አቅም በማሳደግየክልሉን ህዝብ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ።


ዘርፉ የስራ ዕድል በመፍጠር፣ ተኪ ምርትን በማምረትና ቴክኖሎጂን በማሳደግ እንደክልል ለተጀመረው የቤተሰብ ብልጽግና የማረጋገጥ ግብ ሰፊ ድርሻ ያለው ብለዋል።

በዚህም የክልሉ መንግስት ለዘርፉ በሰጠው ትኩረት ጥናትን መሰረት ያደረገ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቁመውበክልሉ ያለው ምቹ መሰረተ ልማት ኢንዱስትሪውን ለማስፋፋት እንደሚያግዝ ገልጸዋል።

በክልሉ ያለውን መሬትና የሰው ሃይል በመጠቀም ምርታማነትን በማሳደግ ለኢንዱስትሪ ግብዓት የሚሆኑ ምርቶች ላይ ማተኮርና ዘርፉን ማስፋፋት ልዩ ትኩረት የሚሰጠው አጀንዳ መሆኑንም ተናግረዋል።


የክልሉ ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ሀላፊ ጎሳዬ ጎዳና በበኩላቸው ቢሮው በክልሉ ያለውን የኢንዱስትሪ አቅም በተገቢው ለመጠቀም በጥናት የተደገፈ ስራ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር የተዘጋጀው የኢንዱስትሪ ፍኖተ ካርታ ስትራቴጂክ እቅድ በክልሉ ያለውን የአምራች ኢንዱስትሪ አቅም በማሳደግ ዘርፈ ብዙ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል።

ዘርፉ የባለድርሻ አካላትን ቅንጅታዊ ስራ የሚጠይቅ በመሆኑ በምክክሩ የተገኙ ግብዓቶችን በማጠናከር ወደ ኢንዱስትሪ የሚደረገውንሽግግር ለማጠናከር በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል።


ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል የክልሉ ውሃ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ሃላፊ ዶክተር ኢንጂነር ከበደ ጋኖሌ ጥናቱ በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ያለውን አቅም ለይቶ መስራት የሚያስችል ነው።

እንደክልል በማዕድን ዘርፍ ያለው ትልቅ አቅም የኢንዱስትሪ ግብዓት የሚሆንና ሰፊ የስራ ዕድል የሚፈጥር በመሆኑ በጥናቱ ትኩረት ሊደረግበት ይገባል ብለዋል።

በጥናቱ የተለዩ የኢንዱስትሪ ክላስተሮች የአካባቢውን አቅም የለዩ መሆናቸው በተለየ ትኩረት እንድንሰራ የሚያስችልና ቅንጅት የሚጠይቅ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ ሃላፊ መምሩ ሞኬ ናቸው።

በግብርናው ዘርፍም አትክልት ተኮር ኢንዱስትሪ ማስፋፋት የሚያስችል አቅም በክልሉ መኖሩን ተናግረዋል።


የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ምርምርና ትብብር ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ታፈሰ ማቲዎስ በበኩላቸው የክልሉ መንግስት ልማትን ለማረጋገጥ ጥናትን መሰረት ያደረገ ስራ መጀመሩ ለሌሎች ክልሎች ተሞክሮ የሚሆን ነው ብለዋል።

በግብርናው ዘርፍ ያለውን አቅም በመጠቀምየግብርና ምርቶችን የሚያቀነባብሩ ኢንዱስትሪዎችን ለማሳደግ ከመድረኩ የተነሱ ግብዓቶችን በማካተት ጥናቱን ውጤታማ ለማድረግ በቅንጅት እንደሚሰሩ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.