
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 4/2017(ኢዜአ)፡- የኦዲት ባለድርሻ አካላት ፎረም የተቋማትን አሰራር በመፈተሽ የቁጥጥር ስርዓትን ለማጠናከርና ተጠያቂነትን ለማስፈን አስቻይ ሁኔታ መፍጠሩን የመንግስት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስታወቀ።
በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኦዲት ባለድርሻ አካላት ፎረም የ2017 በጀት አመት አፈፃፀም ላይ ውይይት አካሒዷል።
የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የሺመቤት ደምሴ (ዶ/ር) የኦዲት ባለድርሻ አካላት ፎረም እቅድ አፈጻጸም ማጠቃለያ ሪፖርት አቅርበዋል።
ቋሚ ኮሚቴው የፌዴራል ተቋማት በመንግስት የተመደበ በጀት አጠቃቀማቸውን፣ ፖሊሲዎች፣ ስትራቴጂዎች፣ ህጎች፣ የአሰራር ስርዓቶችንና እቅዶችን መፈተሽ ላይ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ፎረሙ አስፈጻሚ ተቋማትና ሌሎች ቋሚ ኮሚቴዎች ለኦዲት ሪፖርት የሚሰጡት ትኩረት እንዲጨምር እድል መፍጠሩንም ተናግረዋል።
በዚህም በበጀት ዓመቱ ከኦዲት ግኝት ጋር ተያይዞ አስተያየት ከተሰጣቸው ተቋማት ውስጥ ለሶስት ተቋማት የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ እንዲሁም ለኃላፊዎች የገንዘብ ቅጣት እንዲጣልባቸው ማድረግ መቻሉን ጠቅሰዋል።
በተጨማሪም ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን ጨምሮ ለሰባት የመንግስት ተቋማት የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ እንዲደርሳቸው ተደርጓል ብለዋል።
በበጀት ዓመቱ በተከናወኑ የኦዲት ግኝት ተግባራት ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት መቻሉንም ተናግረዋል።
ይህም የኦዲት ባለድርሻ አካላት ፎረም የተቋማትን አሰራር በመፈተሽ የቁጥጥር ስረዓትን ለማጠናከርና ተጠያቂነትን ለማስፈን አስቻይ ሁኔታ መፍጠሩን ገልጸዋል።
በውይይቱ ላይ የተለያዩ የፌዴራል ተቋማት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026