አዲስ አበባ፤ሰኔ 12/2017(ኢዜአ)፦ችግር ፈቺ የፈጠራ ስራዎች "መፍጠር እና መፍጠን" የሚለውን አገራዊ እሳቤ ከዳር ለማድረስ ጉልህ አስተዋፅኦ እያበረከቱ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጃንጥራር አባይ ገለፁ።
"የሀሳብ ፈጠራ ለብሩህ ነገ" በሚል መሪ ሃሳብ ሲካሔድ የቆየው የንግድ ፈጠራ ሃሳብ ውድድር የማጠቃለያ መርኃ ግብር በዓድዋ ድል መታሰቢያ እየተካሄደ ይገኛል።
የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጃንጥራር አባይ በመርኃ ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልእክት እንደገለጹት፤ በአዲስ አበባ በሶስት ዙሮች በተካሄደው የንግድ ፈጠራ ሃሳብ ውድድር አበረታች ውጤት ተመዝግቧል።
ውድድሩ ወጣቱ ስራ ፈጣሪ፣ ተወዳዳሪና በአገሪቱ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ውስጥ የጎላ ተሳትፎ እንዲኖረው ከማስቻል ባለፈ በቴክኖሎጂ ዘርፍ ያለውን አቅም ለማውጣት እድል ፈጥሯል ብለዋል።
ወጣቶች የሚያመነጯቸውን ችግር ፈቺ የፈጠራ ሃሳቦች በዘላቂነት ጥቅም ላይ ለማዋል በትኩረት እየተሰራበት መሆኑን ጠቅሰዋል።
በተለይም የሚበለጽጉ የፈጠራ ስራዎች ከአገር አልፎ አለም አቀፍ ተፈላጊነት እንዲኖራቸው መስራት ያስፈልጋል ነው ያሉት።
መንግስት በየወቅቱ ጥራታቸው፣ ደህንነታቸውና ችግር ፈቺ መሆናቸው የተረጋገጡና የተመረጡ የፈጠራ ስራዎችን ተግባራዊ ለማድረግ እየሰራ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።
ለአብነትም የሃሳብ ፈጠራ ውድድሩ አንዱ ማሳያ መሆኑን ጠቁመው ይህም "መፍጠርና መፍጠን" የሚለውን አገራዊ እሳቤ ከዳር ለማድረስ ጉልህ አስተዋፅኦ እያበረከተ ይገኛል ነው ያሉት።
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጥራቱ በየነ በበኩላቸው፣ የወጣቶች የፈጠራ ስራዎች የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻል ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑን ተናግረዋል።
የፈጠራ ውጤቶቹ አገር አሻጋሪ ትውልድ እየተፈጠረ መሆኑን በተግባር ያሳያሉ ያሉት ምክትል ከንቲባው የፈጠራ ሃሳብ ውድድሩ ጠቃሚ የፈጠራ ውጤቶች ይፋ የሚደረጉበት መሆኑን አስታውቀዋል።
በውድድሩ የተሳተፉ የፈጠራ ሃሳብ ባለቤቶች በቀጣይ የፋይናንስ አቅርቦትና የገበያ ትስስር የሚፈጠርላቸው መሆኑን አረጋግጠዋል።
በውድድሩ 145 ወጣቶች የተሳተፉ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ 15 ቱ ከተማዋን ወክለው በፌደራል ደረጃ በሚደረጉ ተመሳሳይ ውድድሮች እንደሚሳተፉ ጠቅሰዋል።
እየተካሄደ ባለው ውድድር ምርጥ አምስት ተወዳዳሪዎች ተሸላሚ እንደሚሆኑ ተገልጿል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025