
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 12/2017 (ኢዜአ)፦ በበጀት አመቱ 11 ወራት ከ7 ነጥብ 21 ቢሊየን ዶላር በላይ ገቢ ከወጪ ንግድ መገኘቱን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 38ኛ መደበኛ ስብሰባ የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር የ2017 በጀት ዓመት የ11 ወራት የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ተወያይቷል።

የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) እንደተናገሩት በበጀት አመቱ በሀገሪቱ የወጪ ንግድ ታሪክ ከፍተኛ የሆነ ገቢ ተገኝቷል።
ከጠቅላላ የወጪ ንግድ 4 ነጥብ 59 ቢሊየን ዶላር ለማግኘት ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን አስታውሰው በአፈጻጸም ከእቅድ በላይ 7 ነጥብ 21 ቢሊየን ዶላር ገቢ መገኘቱን ገልጸዋል።
በበጀት አመቱ መጨረሻ ከ 8 ቢሊየን ዶላር በላይ ገቢ ይገኛል ተብሎ እንደሚጠበቅም ጠቁመዋል።
በበጀት አመቱ 11 ወራት ከወጪ ንግድ የተገኘው ገቢ ከ2016 በጀት አመት ጋር ሲነጻጸር ከ 3 ነጥብ 96 ቢሊየን ዶላር በላይ ጭማሪ ማሳየቱንም ጠቅሰዋል።

በማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙ ከተሳኩ ኢኮኖሚያዊ ውጤቶች መካከል የወጪ ንግድ ዘርፍ ከፍተኛ አፈጻጸም እየተመዘገበበት መሆኑንም አክለዋል።
በወጪ ንግድ ምቹ ምህዳር መፈጠሩ፣ የተለያዩ የህግና አሰራር ማነቆዎች መፈታታቸው፣ ከላኪዎች እና ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በተሻለ ቅንጅት በመሰራቱ በአገሪቱ ታሪክ ከፍተኛውን ገቢ ማግኘት ተችሏል ብለዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026