የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ባለፉት 11 ወራት ከወጪ ንግድ ከ7 ነጥብ 21 ቢሊየን ዶላር በላይ ገቢ ተገኘ

Jun 20, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 12/2017 (ኢዜአ)፦ በበጀት አመቱ 11 ወራት ከ7 ነጥብ 21 ቢሊየን ዶላር በላይ ገቢ ከወጪ ንግድ መገኘቱን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ።

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 38ኛ መደበኛ ስብሰባ የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር የ2017 በጀት ዓመት የ11 ወራት የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ተወያይቷል።


የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) እንደተናገሩት በበጀት አመቱ በሀገሪቱ የወጪ ንግድ ታሪክ ከፍተኛ የሆነ ገቢ ተገኝቷል።

ከጠቅላላ የወጪ ንግድ 4 ነጥብ 59 ቢሊየን ዶላር ለማግኘት ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን አስታውሰው በአፈጻጸም ከእቅድ በላይ 7 ነጥብ 21 ቢሊየን ዶላር ገቢ መገኘቱን ገልጸዋል።

በበጀት አመቱ መጨረሻ ከ 8 ቢሊየን ዶላር በላይ ገቢ ይገኛል ተብሎ እንደሚጠበቅም ጠቁመዋል።

በበጀት አመቱ 11 ወራት ከወጪ ንግድ የተገኘው ገቢ ከ2016 በጀት አመት ጋር ሲነጻጸር ከ 3 ነጥብ 96 ቢሊየን ዶላር በላይ ጭማሪ ማሳየቱንም ጠቅሰዋል።


በማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙ ከተሳኩ ኢኮኖሚያዊ ውጤቶች መካከል የወጪ ንግድ ዘርፍ ከፍተኛ አፈጻጸም እየተመዘገበበት መሆኑንም አክለዋል።

በወጪ ንግድ ምቹ ምህዳር መፈጠሩ፣ የተለያዩ የህግና አሰራር ማነቆዎች መፈታታቸው፣ ከላኪዎች እና ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በተሻለ ቅንጅት በመሰራቱ በአገሪቱ ታሪክ ከፍተኛውን ገቢ ማግኘት ተችሏል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ ነው-ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ

ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

May 21, 2026

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026