
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 12/2017(ኢዜአ)፦ የስራ ባህልን በትውልድ ውስጥ ለማስረጽ የሃይማኖት ተቋማት፣ ትምህርት ቤቶች፣ መገናኛ ብዙሃንን ጨምሮ የባለድርሻ አካላት ሚና የላቀ ሊሆን እንደሚገባ የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ።
"የስራ ባህል ምርታማነት ለሀገር ሉዓላዊነት" በሚል መሪ ሃሳብ የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የፓናል ውይይት ተካሂዷል፡፡

በውይይቱ ማጠቃለያ የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል እንዳሉት የስራ ባህል ግንባታ ስኬታማ እንዲሆን ትውልድን ከታች ጀምሮ መቅረጽ ይገባል፡፡
ትውልድን በመቅረጽ የሃይማኖት ተቋማት፣ ትምህርት ቤቶች፣ መገናኛ ብዙሃንን ጨምሮ የባለድርሻ አካላት ሚና የላቀ ሊሆን እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
ለሙያ ያለን አመለካከት የአስተሳሰብ ለውጥ የሚፈልግ ነው ያሉት ሚኒስትሯ ከቤተሰብ ጀምሮ የስራ ባህልን ማዳበር እንደሚያስፈልግ ጠቅሰዋል፡፡
ያሉንን አቅምና ጸጋ መለየት በዛ ላይ ተመስርቶ ፈጠራና ፍጥነትን በማከል ውጤታማ ስራ ማከናወን ይጠበቅብናል ነው ያሉት፡፡
በዚህ ረገድ እንደሀገር መልካም ጅምሮች በመኖራቸው ይህንኑ በማስፋት ለውጤት እንዲበቃ ማድረግ ይገባል ብለዋል፡፡
ምርታማነትን ማሳደግ በሚያስችሉ የቴክኖሎጂና የሰው ሃይል ልማት ላይ ይበልጥ መስራት እንደሚገባ ተነስቷል፡፡
እንደ ኮሪደር ልማትና ህዳሴ ግድብ ያሉ መልካም ተሞክሮዎችን ማስፋት እንደሚገባም ነው የተገለጸው፡፡
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026