የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የስራ ባህልን በትውልድ ውስጥ በማስረጽ በኩል የሃይማኖት ተቋማት፣ ትምህርት ቤቶችና የመገናኛ ብዙሃን ሚና የላቀ ሊሆን ይገባል - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል

Jun 20, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 12/2017(ኢዜአ)፦ የስራ ባህልን በትውልድ ውስጥ ለማስረጽ የሃይማኖት ተቋማት፣ ትምህርት ቤቶች፣ መገናኛ ብዙሃንን ጨምሮ የባለድርሻ አካላት ሚና የላቀ ሊሆን እንደሚገባ የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ።

"የስራ ባህል ምርታማነት ለሀገር ሉዓላዊነት" በሚል መሪ ሃሳብ የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የፓናል ውይይት ተካሂዷል፡፡


በውይይቱ ማጠቃለያ የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል እንዳሉት የስራ ባህል ግንባታ ስኬታማ እንዲሆን ትውልድን ከታች ጀምሮ መቅረጽ ይገባል፡፡

ትውልድን በመቅረጽ የሃይማኖት ተቋማት፣ ትምህርት ቤቶች፣ መገናኛ ብዙሃንን ጨምሮ የባለድርሻ አካላት ሚና የላቀ ሊሆን እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡

ለሙያ ያለን አመለካከት የአስተሳሰብ ለውጥ የሚፈልግ ነው ያሉት ሚኒስትሯ ከቤተሰብ ጀምሮ የስራ ባህልን ማዳበር እንደሚያስፈልግ ጠቅሰዋል፡፡

ያሉንን አቅምና ጸጋ መለየት በዛ ላይ ተመስርቶ ፈጠራና ፍጥነትን በማከል ውጤታማ ስራ ማከናወን ይጠበቅብናል ነው ያሉት፡፡

በዚህ ረገድ እንደሀገር መልካም ጅምሮች በመኖራቸው ይህንኑ በማስፋት ለውጤት እንዲበቃ ማድረግ ይገባል ብለዋል፡፡

ምርታማነትን ማሳደግ በሚያስችሉ የቴክኖሎጂና የሰው ሃይል ልማት ላይ ይበልጥ መስራት እንደሚገባ ተነስቷል፡፡

እንደ ኮሪደር ልማትና ህዳሴ ግድብ ያሉ መልካም ተሞክሮዎችን ማስፋት እንደሚገባም ነው የተገለጸው፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.