
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 12/2017(ኢዜአ)፦ የስራ ባህልን በትውልድ ውስጥ ለማስረጽ የሃይማኖት ተቋማት፣ ትምህርት ቤቶች፣ መገናኛ ብዙሃንን ጨምሮ የባለድርሻ አካላት ሚና የላቀ ሊሆን እንደሚገባ የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ።
"የስራ ባህል ምርታማነት ለሀገር ሉዓላዊነት" በሚል መሪ ሃሳብ የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የፓናል ውይይት ተካሂዷል፡፡

በውይይቱ ማጠቃለያ የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል እንዳሉት የስራ ባህል ግንባታ ስኬታማ እንዲሆን ትውልድን ከታች ጀምሮ መቅረጽ ይገባል፡፡
ትውልድን በመቅረጽ የሃይማኖት ተቋማት፣ ትምህርት ቤቶች፣ መገናኛ ብዙሃንን ጨምሮ የባለድርሻ አካላት ሚና የላቀ ሊሆን እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
ለሙያ ያለን አመለካከት የአስተሳሰብ ለውጥ የሚፈልግ ነው ያሉት ሚኒስትሯ ከቤተሰብ ጀምሮ የስራ ባህልን ማዳበር እንደሚያስፈልግ ጠቅሰዋል፡፡
ያሉንን አቅምና ጸጋ መለየት በዛ ላይ ተመስርቶ ፈጠራና ፍጥነትን በማከል ውጤታማ ስራ ማከናወን ይጠበቅብናል ነው ያሉት፡፡
በዚህ ረገድ እንደሀገር መልካም ጅምሮች በመኖራቸው ይህንኑ በማስፋት ለውጤት እንዲበቃ ማድረግ ይገባል ብለዋል፡፡
ምርታማነትን ማሳደግ በሚያስችሉ የቴክኖሎጂና የሰው ሃይል ልማት ላይ ይበልጥ መስራት እንደሚገባ ተነስቷል፡፡
እንደ ኮሪደር ልማትና ህዳሴ ግድብ ያሉ መልካም ተሞክሮዎችን ማስፋት እንደሚገባም ነው የተገለጸው፡፡
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026