
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 12/2017(ኢዜአ)፦ የባህር በር ለኢትዮጵያ የፖለቲካ አጀንዳ ሳይሆን የህልውናዋ ጉዳይ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከመላው ኢትዮጵያ ከተውጣጡ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ጋር ውይይት አድርገዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የኢትዮጵያ የሁልጊዜም ፍላጎት ከጎረቤቶቿ ጋር በጋራ መልማት መሆኑን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ሰላም መሆንና መልማት ለቀጣናው ዕድገት በጎ ሚና እንደሚጫወትም ጨምረው ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ ትልቅ ሀገር እና ከፍተኛ የህዝብ ብዛት አላት ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሰላም እና ልማት ለኢትዮጵያ ቁልፍ ጉዳዮች እንደሆኑ ጎረቤቶቿ ሊረዱ እንደሚገባ አመልክተዋል።

ኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄዋ በህጋዊ እና ሰላማዊ መንገድ ምላሽ እንዲያገኝ እየሰራች እንደምትገኝም ተናግረዋል።
የባህር በር ጉዳይ የፖለቲካ አጀንዳ አይደለም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉዳዩ ለኢትዮጵያ የህልውና ጉዳይ ነው ብለዋል።
የባህር በር አለመኖር በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ጫና እያሳደረ እንደሚገኝ ገልጸው ጉዳዩ አፈጣኝ መፍትሄ እንደሚያሻው አመልክተዋል።

ኢትዮጵያ የባህር በር እንደሚፈያስፈልጋት እና ይህም በንግድ ህጎች አማካኝነት ምላሽ ያገኛል ብለው እንደሚያምኑም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
የጎረቤት ሀገራት የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ በቀናነት እንዲረዱትና ጥያቄው ከመልማት እና ከማደግ ካለ ጽኑ ፍላጎት የመነጨ እንደሆነ መገንዘብ እንደሚገባቸው አንስተዋል።
ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
May 21, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026