የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በክልሉ አምራች ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያጎለብቱ ተግባራት እየተከናወኑ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ

Jun 20, 2025

IDOPRESS

ሰመራ፤ ሰኔ 12/2017(ኢዜአ)፦ በአፋር ክልል አምራች ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያጎለብቱ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ አስታወቁ።

በአፋር ክልል በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የተገነቡ አምራች ኢንዱስትሪዎች ተመርቀው ወደ ስራ እየገቡ ነው።


ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ በሎጊያ ከተማ በ159 ሚሊየን ብር የተገነቡ የተፈጥሮ ምንጭ ውሃና የዱቄት ፋብሪካዎችን ዛሬ መርቀው ስራ አስጀምረዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንደገለፁት በክልሉ አምራች ኢንዱስትሪዎች ወደ ስራ ገብተው የስራ ዕድል መፍጠር እንዲችሉ እየተሰራ ነው።

አሁን ላይ ወደ ስራ እየገቡ ያሉት ፋብሪካዎች የስራ ዕድልን ከመፍጠራቸው ባሻገር የስራ ባህል እንዲያድግ አስተዋፅኦ እያደረጉ ነው ብለዋል።

አምራች ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያጎለብቱ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑንም ነው የተናገሩት።

የክልሉ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ሀላፊ ወይዘሮ ኤይሻ ያሲን በበኩላቸው በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አማካኝነት በርካታ ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት መግባታቸውን ገልጸዋል።

በዚህ ዓመት ይመረቃሉ ተብለው በዕቅድ ከተያዙት አስር ፋብሪካዎች መካከል ስድስቱ ለአገልግሎት መብቃታቸውን ገልጸው ቀሪዎቹ በቀጣይ ወራት ውስጥ ተመርቀው ለአገልግሎት ይበቃሉ ብለዋል።


ዛሬ ከተመረቁት ፋብሪካዎች መካከል 'አዋሽ' የማዕድን ውሃ ፋብሪካ ባለቤት እና ስራ አስኪያጅ ኢብራሂም ሰኢድ፤ ፋብሪካው በ119 ሚለየን ብር መገንባቱን ገልጸዋል።

ፋብሪካው ለ150 ሰዎች የስራ ዕድል የፈጠረ መሆኑንም ጨምረው ተናግረዋል።

የሉሲ ዱቄት ፋብሪካ ባለቤትና ስራ አስኪያጅ ኢብራሂም መሐመድ ሰኢድ በበኩላቸው ፋብሪካው በ40 ሚሊየን ብር መገንባቱን ጠቅሰው በቀን 260 ኩንታል ዱቄት የማምረት አቅም አለው ብለዋል።

ለአካባቢው ነዋሪዎች የስራ ዕድል መፍጠሩን ጠቁመው በቀጣይነት የመኮረኒና ፓስታ ፋብሪካ ለማስፋት ዕቅድ እንዳላቸው ገልጸዋል።

በፋብሪካው በተፈጠረልኝ የስራ ዕድል ራሴንና ቤተሰቤን መጥቀም ችያለሁ ያሉት ደግሞ የሎጊያ ከተማ ነዋሪ ወይዘሮ ፋጡማ አብደላ ናቸው።

በምረቃ ስነ-ስር'ቱ ላይ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና የሎጊያ ከተማ ነዋሪዎች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.