ጅግጅጋ፤ ሰኔ 13/2017(ኢዜአ)፦ በክልሉ የመንግሥት የፋይናንስና የንብረት አስተዳደርን በዲጂታል ቴክኖሎጂና ቀልጣፋ አሰራር የታገዘ መሆኑን የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ አስታወቀ።
ከሀገራዊ ለውጡ በኋላ በሶማሌ ክልል ያለውን የመንግሥት የፋይናንስና የንብረት አስተዳደር አሰራርን በተመለከተ የክልሉ የፋይናንስ ቢሮ ሃላፊ ደይብ አህመድኑር ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸውም የፋይናንስ አስተዳደር ማሻሻያ ስራ በትክክል ለውጥ ያመጣ እና ውጤትም የተመዘገበበት መሆኑን አብራርተዋል።
የበጀት አስተዳደር አዋጅ እና ለተፈጻሚነቱ የሚያገለግሉ 10 የህግ ማቀፎች ተዘጋጅተው በመተግበር ላይ መሆናቸውን አንስተዋል።
የመንግሥትን የፋይናንስና የንብረት አስተዳደር ስርዓት በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ እየተደረገ መሆኑንና በዚህም የላቀ ውጤት መምጣቱን ተናግረዋል።
የመንግሥት ፋይናንስና የንብረት የመረጃ አያያዝ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ ዘመናዊ አሰራርን እየተከተለ መሆኑንም ገልጸዋል።
ከሰባት አመታት በፊት የክልሉ በጀት 15 ቢልዮን ብር እንደነበር አስታውሰው አሁን ላይ 41 ቢልዮን ብር መድረሱን አስታውቀዋል።
ከበጀቱም 60 በመቶው ለድህነት ቅነሳ የሚያገለግሉ የልማት ስራዎች ላይ እየዋለ መሆኑን ጨምረው አስረድተዋል።
በክልሉ የገቢ መሰብሰብ አቅምም ከለውጡ በፊት ከነበረበት ከ12 በመቶ ከፍተኛ እድገት አሳይቶ አሁን ላይ 43 በመቶ ደርሷል ብለዋል።
የሲቪክ ማህበረሰብ ድርጅቶች የሆኑ የልማት ድርጅቶች ኢንተርፕራይዞች እና የበጎ አድራጎት ድርጅቶች በጀት አስተዳዳር አዋጅ ተግባራዊ ለማድረግ እየተሠራ መሆኑንም አብራርተዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025