
ጎንደር፤ ሰኔ 14/2017(ኢዜአ)፡- በጎንደር ከተማ እየተጠናቀቀ ባለው በጀት ዓመት ከአንድ ነጥብ ስምንት ቢሊዮን ብር በላይ ግብር መሰብሰብ መቻሉን የከተማ አስተዳደሩ ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ።
የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋዮች ከመጪው ሐምሌ ጀምሮ በዲጂታል ስርዓት ግብራቸውን የሚከፍሉበት አሰራር ለመተግበር የሚያስችል የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ዛሬ ተካሂዷል።

የመምሪያው ሃላፊ ወይዘሮ ጥሩዬ አታክልት በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፤ የከተማው የንግድ እንቅስቃሴ የሚያመነጨውን ገቢ በመሰብሰብ ለልማትና መልካም አስተዳደር ስራዎች ለማዋል ትኩረት ተሰጥቶ ሲሰራ ቆይቷል።
በዚህም በጀት ዓመት እስካሁን ከአንድ ነጥብ ስምንት ቢሊዮን ብር በላይ ግብር በመሰብሰብ ለከተማዋ ልማት መፋጠን ማዋል መቻሉን አስታወቀዋል።
የተሰበሰበው ገቢም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ350 ሚሊዮን ብር ብልጫ ያለው መሆኑን አስረድተዋል።
ለገቢው ማደግም በበጀት ዓመቱ ከሁለት ሺህ በላይ አዳዲስ ግብር ከፋዮች ወደ ግብር መረቡ እንዲቀላቀሉ መደረጉ አስተዋጽኦው ከፍ ያለ ነው ብለዋል።

የገቢ አሰባሰቡን ለማሻሻልም ዲጅታላይዜሽንን እስከ ታች ድረስ በመተግበር ለግብር ከፋዩ ከቀድሞ የተሻለ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
በሐምሌ 2017 ዓ.ም ጀምሮ የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋዮች ባሉበት ሆነው በዲጂታል የግብር ክፍያ ስርዓት የሚጠበቅባቸውን ግብር እንዲከፍሉ ዝግጅት እየተደረገ እንደሚገኝ አንሰተዋል።
በዲጂታል የግብር ክፍያ ስርዓቱ ከ14ሺ በላይ የደረጃ "ሐ " ግብር ከፋዮች መካተታቸውን ጠቁመው፤ የግብር ከፋዮች መረጃዎችንም ዲጂታላይዝ የማድረግ ስራዎች መከናወናቸውን አስረድተዋል።
በከተማው የልማት ስራዎችን በማጠናቀቅ የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የግብር አሰባሰቡን ማዘመን እንደሚገባ የገለጹት ደግሞ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የከተማ አስተዳደሩ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ሃላፊ አቶ ግርማይ ልጃለም ናቸው።

በከተማው የሰፈነው ሠላም በርካታ የልማት እቅዶችን ለማከናወን ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ጠቁመው፤ የግብር ክፍያ ስርዓቱን ለማዘመን የተጀመሩ የዲጂታል ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።
በጎንደር የአዘዞ ጠዳ ክፍለ ከተማ ገቢዎች ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ደስታው ሙሉነህ፤ ዲጂታል የግብር ክፍያ ስርዓት የመንግስትን ግብር አሟጦ ለመሰብሰብ ምቹ መደላደል የሚፈጥር ነው ብለዋል።
በመድረኩ በየደረጃው የሚገኙ የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች፣ የገቢ ተቋሙ ባለሙያዎችና አጋር አካላት ተሳትፈዋል።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026