
ጎንደር ፤ ሰኔ 17/2017(ኢዜአ)፡- በማዕከላዊ ጎንደር ዞን የጣና ሃይቅ ገባር ወንዞች በክረምቱ ወራት የሚያስከትሉትን የጎርፍ አደጋ መከላከል የሚያስችል 16 ኪሎ ሜትር የአፈር ግድብ ስራ መከናወኑን የዞኑ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ተጠሪ ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።
የጽሕፈት ቤቱ ሃላፊ አቶ ኑረዲን ሰኢድ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የጎርፍ ቅድመ መከላከል ስራው የተከናወነው በዞኑ የጣና ሀይቅ አዋሳኝ በሆኑት በምስራቅና ምዕራብ ደንቢያ ወረዳዎች በ6 ቀበሌዎች ውስጥ ነው፡፡
ባላፉት ሶስት ወራት በተከናወነው የጎርፍ መከላከል ስራ ድርማና ዳህና በተባሉ የጣና ሀይቅ ገባር ወንዞች ላይ በክልሉ መንግስት 10 ሚሊዮን ብር በጀት የአፈር ግድብ ስራ ማከናወን መቻሉን አውስተዋል።

በማሽነሪዎችና በህብረተሰቡ የጉልበት ተሳትፎ በተከናወነው የጎርፍ መከላከል ስራ በወንዞቹ ግራና ቀኝ ከፍታቸው አስከ አራት ሜትር የሆኑ የጎርፍ መከላከያ የአፈር ግድቦች መሰራታቸውን ተናግረዋል፡፡
የጎርፍ ቅድመ መከላከል ስራው በአካባቢዎቹ 960 አባወራዎችና እማወራዎችን፣ 3ሺህ ሄክታር የሚጠጋ የእርሻ ማሳንና 16ሺህ የሚጠጉ የቤት እንስሳትን ከአደጋ መታደግ የሚያስችል መሆኑንም ተናግረዋል።
የአፈር ግድቡ ዘላቂ አገልግሎት እንዲሰጥም በየዓመቱ ችግኝ ተከላን ጨምሮ በስነ ህይወታዊ ዘዴዎች የማጠናከር ስራ እየተከናወነ መሆኑን አስረድተዋል።
የዳህና ወንዝ ክረምት በገባ ቁጥር ሰብሮ በመውጣት በመኖሪያ ቤታችንና በእርሻ ማሳችን ላይ ሰፊ ጉዳት ያደርስብን ነበር ያሉት ደግሞ በምዕራብ ደንቢያ ወረዳ የዋዋ ቀበሌ ነዋሪ አቶ ታምራት ግዛቸው ናቸው፡፡
በየዓመቱ የሚከናወኑ የጎርፍ መከላከያ ግድቦች ከስጋት እየታደጓቸው መሆኑን ጠቁመው፤ ዘንድሮም ተመሳሳይ ተግባር በመከናወኑ ስጋት እንደሌለባቸው ተናግረዋል።

በምስራቅ ደንቢያ ወረዳ የጃንጓ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ጎሹ መልካሙ፤ የድርማ ወንዝ በየዓመቱ በሚያስከትለውን የጎርፍ መጥለቅለቅ አደጋ ለመቀነስ የመከላከያ ክትር መሰራቱ መልካም ነው ብለዋል።
የጎርፍ መከላከያ ግድቡ ዘላቂነት እንዲኖረውም ከህብረተሰቡ ጋር በመሆን የአፈርና ውሃ እቅባ ስራ እያከናወኑ እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡
በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ክረምቱን ተከትሎ ሊከሰቱ የሚችሉ የተፈጥሮ አደጋዎችን መከላከልና ፈጣን ድጋፍ ለመስጠት የሚያስችል አብይ ኮሚቴ ተቋቁሞ እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026