
ሮቤ፤ ሰኔ 19/2017 (ኢዜአ ) በባሌ ዞን የልማት ፕሮጀክቶችን በተሻለ ፍጥነትና ጥራት በማጠናቀቅ ለህብረተሰቡ ተጠቃሚነት እንዲውሉ እየተደረገ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብዱልሀኪም አልይ ገለጹ።
የክልሉ እና የዞኑ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች በባሌ ዞን የተለያዩ ወረዳዎች ውስጥ ከ1 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነቡ 160 የልማት ፕሮጀክቶችን የማስመረቁ ሂደት እንደቀጠለ ነው።
በዛሬው ዕለትም በጎባና ዲንሾ ወረዳዎች ተገንብተው ለአገልግሎት የበቁ የ''ቡኡረ ቦሩ'' የተሰኘ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ማብለያ ማዕከል፣ ድልድይ፣ የገጠር መንገድና ሌሎች ፕሮጀክቶች ተመርቀዋል።

የባሌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብዱልሀኪም አልይ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፣ በዞኑ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችን በተሻለ ፍጥነትና ጥራት በማጠናቀቅ ለህብረተሰቡ ተጠቃሚነት እንዲውሉ እየተደረገ ነው።
በዞኑ የተለያዩ ወረዳዎች ውስጥ ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ ተገንብተው ለአገልግሎት የበቁት 160 የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች የዚሁ ጥረት አካል መሆናቸውን ተናግረዋል።

በተለይ ፕሮጀክቶቹ የአርሶ አደሩን የትምህርት ተደራሽነትና ጤናውን በማሻሻል በኩል አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ በመሆናቸው ልዩ ያደርጋቸዋል ብለዋል።
እንዲሁም አርሶ አደሩ ምርቱን በቀላሉ ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚነቱ ይበልጥ እንዲረጋገጥ የሚያግዙ የገጠር መንገድና የድልድይ ግንባታ እንደሚገኝበት አክለዋል።
በምረቃ መርሓ ግብሩ ላይ የተገኙት የኦሮሚያ መስኖና አርብቶ አደር ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ሮባ ቱርጬ በበኩላቸው የክልሉ መንግሥት ከለውጡ ማግስት ጀምሮ የህዝቡን የመሰረተ ልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ እየመለሰ ነው።

በተለይ የልማት ፕሮጀክቶቹ የህዝብን የመሰረተ ልማት ጥያቄዎች ከመመለስ ባሻገር ተጠቃሚነቱን ይበልጥ ማሳደግ እንዲችሉ ታስቦ የተገነቡ መሆናቸውንም አመልክተዋል።
መንግስት የህብረተሰቡን ህይወት ለመለወጥ የሚያደርገው ጥረት እንዲሳካ ህዝቡም የአካባቢውን ሰላምና ደህንነት ይበልጥ መጠበቅና ለልማት ፕሮጀክቶቹ እንክብካቤ እንዲያደርግም አቶ ሮባ ጠይቀዋል።

በወረዳው የህብረተሰቡ የረዥም ጊዜ ጥያቄ የነበሩ 24 የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ከ65 ሚሊዮን ብር ወጪ ተገንብተው ለአገልግሎት መብቃታቸውን የገለጹት ደግሞ የጎባ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ አብዱልቃድር ኡስማን ናቸው።
ከወረዳው ነዎሪዎች መካከል አቶ ሁሴን አህመድ በሰጡት አስተያየት የፕሮጀክቶቹ መገንባት መንግስት ለህዝቡ የገባውን ቃል ጊዜውን ጠብቆ እንደሚመልስ ማሳያዎች ናቸው ብለዋል።

በተለይ የቅድመ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቱ ግንባታ ልጆቻቸው ከአካባቢያቸው ሳይርቁ የዕድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ስለሚያደርግ በሂደቱ የተሳተፉ አካላትን አመስግነዋል።
በባሌ ዞን በተለያዩ ወረዳዎች ውስጥ የተገነቡ ፕሮጀክቶችን የማስመረቁ ሂደት እንደሚቀጥል ከመርሐ ግብሩ ለመረዳት ተችሏል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026