የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የምስራቅ አፍሪካ የስልጠና ልህቀት ማዕከል ለመሆን የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ ነው

Jul 1, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ ፤ ሰኔ 22/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ የውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት በምስራቅ አፍሪካ የስልጠና ልህቀት ማዕከል ለመሆን የሚያስችል የአቅም ግንባታ እና ሎጂስቲክስ የማሟላት ስራ እያከናወነ መሆኑን አስታወቀ።

የኢትዮጵያ የውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ታመነ ሀይሉ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ የአቅም ግንባታ ስራ ኢንስቲትዩቱ ከሚያከናውናቸው ተግባራት መካከል አንደኛው ነው።

ኢንስቲትዩቱ በዘርፉ ያለውን ችግር በመለየት ስልጠና እየሰጠ መሆኑንና እስካሁን ባለው ከ18 አገራት ለተውጣጡ ከ200 በላይ ባለሙያዎች ስልጠና መስጠቱን ተናግረዋል።

ኢንስቲትዩቱ በዘርፉ የምስራቅ አፍሪካ የስልጠና ልህቀት ማዕከል የመሆን ርዕይውን ለማሳካት እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።

ኢንስቲትዩቱ በዘርፉ ያሉ ችግሮችን በጥናት በመለየት መፍትሄ ከማበጀት ባለፈ ዘመናዊ ላቦራቶሪ እየገነባ መሆኑንም ነው የገለጹት።

በውሃ ዘርፍ ላይ ስልጠና ለሚሰጡ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት አስፈላጊውን ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ጠቁመው በአመት የሚያሰለጥናቸው ባለሙያዎች ቁጥር እያደገ መምጣቱንም አብራርተዋል።

ኢንስቲትዩቱ ከ10 አመት በፊት በአመት 150 የሚጠጉ ባለሙያዎችን ያሰለጥን እንደነበር አንስተው አሁን ላይ ከ2ሺህ በላይ ሰልጣኞችን በአመት እየተቀበለ መሆኑን ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ የውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት አገልግሎቱን በማስፋት ዘርፉ የሚፈልገውን ድጋፍ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።

የኢንስቲትዩቱ ላቦራቶሪ አለም አቀፍ እውቅና ለማግኘት ሰነድ መዘጋጀቱን ገልፀው፤ የልህቀት ማዕከል ለመሆን የሚያስችለውን ስራ እያከናወነ ነውም ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026

‎ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ተወዳዳሪነቷን ለማሳደግ ርብርብ እየተደረገ ነው 

‎ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...

Apr 20, 2026