በና-ፀማይ፤ሰኔ 23/2017(ኢዜአ)፦ በዝናብ አጠር አካባቢዎች የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያስችል የዕቀባ እርሻን በማስፋፋት የመሬት ለምነትንና የውሃ ትነትን ለመቀነስ እየተሰራ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ገለጸ።
በደቡብ ኦሞ ዞን በና-ፀማይ ወረዳ በጎልዲያ ቀበሌ በዕቀባ እርሻ የተከናወነ የግብርና ልማት የመስክ ምልከታና የልምድ ልውውጥ መረሃ ግብር ተካሄዷል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ እና የእርሻ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አድማሱ አወቀ በወቅቱ እንዳሉት የዕቀባ እርሻ (Conservation Agriculture) ዝናብ አጠር በሆኑ አካባቢዎች ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ሚናው የጎላ ነው።
ሰብሎችን አፈራርቆ በመዝራት፣ የሰብል ተረፈ-ምርቶችን በመጎዝጎዝ የውሃ ትነትን ለመቀነስ እና የውሃ ስርገትን በመጨመር የሚከናወነው የዕቀባ እርሻ ተግባር ምርታማነትን ለመጨመር ያስችላል ብለዋል።
የግብርና ቴክኖሎጂው የግሪን ሀውስ ጋዞችን በመቀነስ የአየር ብክለትን ለመከላከልና የአፈር አሲዳማነትንም በመቀነስ ለምነትን ማሻሻል የሚያስችል ምርታማነት እንዲጠመር ያግዛል ሲሉ ገልፀዋል።
በቀጣይም ቴክኖሎጂውን በክልሉ በተመረጡ አካባቢዎች የማላመድና የማስፋፋት ስራ እንደሚሰራም አመላክተዋል ።
የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ በበኩላቸው ቴክኖሎጂው የአርብቶ አደሩን የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተጀመሩ የግብርና ልማት ስራዎችን ውጤታማ ያደርጋል ብለዋል።
የኃይለማርያም እና ሮማን ፋውንዴሽን የዕቀባ እርሻን በበና-ፀማይ ወረዳ ለማስፋፋት ያደረገው ተግባር በዞኑ በሁሉም አካባቢዎች ለማላመድ እንደሚሰራም ተናግረዋል።
የኃይለማርያም እና ሮማን ፋውንዴሽን ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ ሶስና ኃይለማርያም (ዶ/ር) በበኩላቸው በደቡብ ኦሞ ዞን ሐመር እና በና- ፀማይ ወረዳዎች በ40 አርሶ አደር እና አርብቶ አደር ማሳዎች ላይ ቴክኖሎጂውን የማላመድ ስራ ሲሰራ መቆየቱን ገልጸዋል ።
በፋውንዴሸኑ የግብርና ትራንስፎርሜሽን፣ የምግብና ሥነ-ምግብ ዋስትና ፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ ተስፋዬ ፈላሀ በበኩላቸው፥ ቴክኖሎጂው የአፈር መሸርሸርን በመከላከል በአፈር ውስጥ ያሉ ንጥረ-ነገሮችን ለመጠበቅ ያስችላል ብለዋል።
በተለይ የአየር ንብረት ለውጡን ተከትሎ የሚመጣውን ጫና ለመከላከል ያለው ፋይዳ ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰው፤ እንደ ደቡብ ኦሞ ዞን ላሉ ዝናብ አጠር ቆላማ አካባቢዎች ተስማሚና ተመራጭ መሆኑን አረጋግጠዋል ።
የበና-ፀማይ ወረዳ የጎልዲያ ቀበሌ አርሶ አደር ኤርሚያስ አድነው፥ በፋውንዴሽኑ እና በግብርና ባለሙያዎች ምክረ-ሀሳብ መሰረት ቴክኖሎጂውን በማሳቸው ላይ ተግባራዊ ሲያደርጉ መቆየታቸውን ተናግረዋል ።
ይህም የበቆሎ ሰብላቸውን ምርታማነት በማሳደግ፣ አረምን በመቆጣጠርና የሰብል እድገትን በማፋጠን ምርታማነታቸው እንዲጨምር ማድረጉን አንስተዋል።
ሌላው አስተያየት ሰጪ አርሶ አደር ማቲዮስ ገርሾ በበኩላቸው ቴክኖሎጂው ቀደም ሲል በማሳቸው አጋጥሞ የነበረውን የአፈር ለምነት የመቀነስ ችግር የፈታ መሆኑን ገልፀዋል።
እንደ አርሶ አደሩ ገለፃ የሚያገኙትን ጥቂት ምርት የእቀባ እርሻን ተግባራዊ በማድረጋቸው ምርታማነታቸው ጨምሯል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025