
አዳማ ፤ሰኔ 23/2017 (ኢዜአ)፡-የእንስሳት ጤና ኤክስቴንሽንን ውጤታማ በማድረግ የእንስሳት ዘርፍ ልማቱን ለማዘመን ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር ገለፀ።
የእንስሳት ጤና ኤክስቴንሽን ፓኬጅ መመሪያና ፕሮግራም ለክልሎችና ባለድርሻ አካላት የማስተዋወቅ መድረክ በአዳማ ተካሄዷል።

የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ (ዶ/ር) በተለይ ለኢዜአ እንደገለፁት የእንስሳት ሀብት ልማቱን ለማዘመን ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ።
በተለይ በሌማት ትሩፋት ፕሮግራም የወተት ላሞች ዝሪያን ከማሻሻል ጀምሮ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
በዚህም በወተት ላሞች ማዳቀል፤ የተሻለ ምርት በሚሰጡ በዘመናዊ የዶሮና ዓሣ እርባታ፤ እንዲሁም በንብ ልማት ላይ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።

ይሁን እንጂ ከጤና አንፃር የእንስሳት ሀብት ጥራት፣ ደህንነትና ምርታማነትን ለማረጋገጥ የእንስሳት ኤክስቴንሽን ስትራቴጂ ተቀርጾ ወደ ተግባር መገባቱን ገልጸዋል።
ለዚህም የእንስሳት ጤና ፓኬጅ፣ መመሪያና ፕሮግራም መዘጋጀቱን ሚኒስትር ዴኤታው ገልፀው ለተፈፃሚነቱ በቅንጅት ለመረባረብ መድረኩ መሰናዳቱን ጠቁመዋል።
የእንስሳት ጤና ኤክስቴንሽን ፓኬጅ የዘርፉን ልማት ከማዘመንና ምርታማነቱን ከማሳደግ አኳያ ወሳኝ ሚና እንዳለውም ተናግረዋል።

ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል የኦሮሚያ ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ቶሌራ ደበላ በበኩላቸው የእንስሳት ጤና ኤክስቴንሽን ፓኬጁ የዘርፉን ልማት ለማዘመን የጎላ ፋይዳ አለው ብለዋል።
በክልሉ የወተት ላሞች፣ የዶሮ፣ የዓሣ፣ የንብና የስጋ እንሳሳት ኢንሼቲቮች ተቀርፆ ተግባራዊ እየተደረጉ ናቸው ያሉት አቶ ቶሌራ በዚህም በክልሉ የእንስሳት ሀብት ልማትና ዕድገት ላይ ተጨባጭ ውጤት እየመጣ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
የእንስሳት ጤና ኤክስቴንሽን ፓኬጅና ፕሮግራምን ከክልል እስከ ወረዳና ቀበሌ ድረስ በማውረድ ለመተግበርና ውጤታማነቱን እውን ለማድረግ በቁርጠኝነት እንደሚሰራም ምክትል ቢሮ ኃላፊው አረጋግጠዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026