የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የእንስሳት ዘርፍ ልማቱን ለማዘመን ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ ናቸው-- የግብርና ሚኒስቴር

Jul 1, 2025

IDOPRESS

አዳማ ፤ሰኔ 23/2017 (ኢዜአ)፡-የእንስሳት ጤና ኤክስቴንሽንን ውጤታማ በማድረግ የእንስሳት ዘርፍ ልማቱን ለማዘመን ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር ገለፀ።

የእንስሳት ጤና ኤክስቴንሽን ፓኬጅ መመሪያና ፕሮግራም ለክልሎችና ባለድርሻ አካላት የማስተዋወቅ መድረክ በአዳማ ተካሄዷል።


የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ (ዶ/ር) በተለይ ለኢዜአ እንደገለፁት የእንስሳት ሀብት ልማቱን ለማዘመን ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ።

በተለይ በሌማት ትሩፋት ፕሮግራም የወተት ላሞች ዝሪያን ከማሻሻል ጀምሮ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።

በዚህም በወተት ላሞች ማዳቀል፤ የተሻለ ምርት በሚሰጡ በዘመናዊ የዶሮና ዓሣ እርባታ፤ እንዲሁም በንብ ልማት ላይ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።


ይሁን እንጂ ከጤና አንፃር የእንስሳት ሀብት ጥራት፣ ደህንነትና ምርታማነትን ለማረጋገጥ የእንስሳት ኤክስቴንሽን ስትራቴጂ ተቀርጾ ወደ ተግባር መገባቱን ገልጸዋል።

ለዚህም የእንስሳት ጤና ፓኬጅ፣ መመሪያና ፕሮግራም መዘጋጀቱን ሚኒስትር ዴኤታው ገልፀው ለተፈፃሚነቱ በቅንጅት ለመረባረብ መድረኩ መሰናዳቱን ጠቁመዋል።

የእንስሳት ጤና ኤክስቴንሽን ፓኬጅ የዘርፉን ልማት ከማዘመንና ምርታማነቱን ከማሳደግ አኳያ ወሳኝ ሚና እንዳለውም ተናግረዋል።


ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል የኦሮሚያ ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ቶሌራ ደበላ በበኩላቸው የእንስሳት ጤና ኤክስቴንሽን ፓኬጁ የዘርፉን ልማት ለማዘመን የጎላ ፋይዳ አለው ብለዋል።

በክልሉ የወተት ላሞች፣ የዶሮ፣ የዓሣ፣ የንብና የስጋ እንሳሳት ኢንሼቲቮች ተቀርፆ ተግባራዊ እየተደረጉ ናቸው ያሉት አቶ ቶሌራ በዚህም በክልሉ የእንስሳት ሀብት ልማትና ዕድገት ላይ ተጨባጭ ውጤት እየመጣ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

የእንስሳት ጤና ኤክስቴንሽን ፓኬጅና ፕሮግራምን ከክልል እስከ ወረዳና ቀበሌ ድረስ በማውረድ ለመተግበርና ውጤታማነቱን እውን ለማድረግ በቁርጠኝነት እንደሚሰራም ምክትል ቢሮ ኃላፊው አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.