🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ መስከረም 19/2018(ኢዜአ)፡- የአዲስ አበባ የተርሚናል ኢንተርፕራይዝ ማኅበራት የተሳለጠ የትራንስፖርት ፍሰት እንዲፈጠር እያደረጉ እንደሚገኝ የከተማ አስተዳደሩ የትራንስፖርት ቢሮ አስታወቀ።
የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ ያብባል አዲስ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የነዋሪዎችን የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት የአቅርቦት ፍላጎት ለማሳለጥ የተሻለ የአሰራር ሥርዓት እየተፈጠረ ነው።
የመንገድ ደኅንነትና የትራፊክ መጨናነቅን ለመቀነስም ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር በቅንጅት እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
ከዚህ በፊት የታክሲ ተራ አስከባሪ በመባል የሚታወቀውን አደረጃጀት በአዲስ መልክ በተደራጀው የተርሚናል ኢንተርፕራይዝ አማካኝነት የተሻለ የትራንስፖርት አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑን አንስተዋል።
በተርሚናል ኢንተርፕራይዝ የተደራጁ አስተባባሪዎችም የትራፊክ መጨናነቅና የተሳፋሪዎችን እንግልት በመቀነስ የተሳለጠ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ በመፍጠር ጉልህ ፋይዳ እያበረከቱ መሆኑን ገልጸዋል።
በአዲሱ የትራንስፖርት አስተባባሪዎች የተርሚናል ኢንተርፕራይዝም ግልጽና የአሰራር ሥርዓትን በተከተለ አግባብ በ87 ማኅበራት በማደራጀት የተሻለ አገልግሎት የሚሰጡበት ሁኔታ መፈጠሩን አስረድተዋል።
በአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ አማካኝነት በአዲስ በተዋቀረው የተርሚናል ኢንተርፕራይዝ የተደራጁ አስተባባሪዎችም የክህሎት ስልጠና ተሰጥቷቸው ወደስራ እንዲሰማሩ መደረጉን ገልጸው፤ የሚሰበስቡት ገንዘብ ዘመናዊ የአሰራር ሥርዓትን የተከተለ መሆኑን ተናግረዋል።
የኢንተርፕራይዝ ማኅበራት አባላቱም ለሁለት ዓመታት በሚኖራቸው ቆይታ ዕድገት ተኮር በሆኑ ዘርፎች የሚሸጋገሩበት የቁጠባ ሥርዓት መዘርጋቱን አብራርተዋል።
በመዲናዋ የተደራጁ የተርሚናል ኢንተርፕራይዝ ማኅበራትም የነዋሪዎችን የትራንስፖርት አገልግሎት በማሳለጥ ምቹ የትራፊክ ፍሰት በመፍጠር አዎንታዊ ሚና እየተወጡ መሆኑን ገልጸዋል።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026