የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የተርሚናል ኢንተርፕራይዝ ማኅበራት የተሳለጠ የትራንስፖርት ፍሰት እንዲፈጠር እያደረጉ ነው 

Sep 30, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መስከረም 19/2018(ኢዜአ)፡- የአዲስ አበባ የተርሚናል ኢንተርፕራይዝ ማኅበራት የተሳለጠ የትራንስፖርት ፍሰት እንዲፈጠር እያደረጉ እንደሚገኝ የከተማ አስተዳደሩ የትራንስፖርት ቢሮ አስታወቀ።

የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ ያብባል አዲስ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የነዋሪዎችን የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት የአቅርቦት ፍላጎት ለማሳለጥ የተሻለ የአሰራር ሥርዓት እየተፈጠረ ነው።

የመንገድ ደኅንነትና የትራፊክ መጨናነቅን ለመቀነስም ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር በቅንጅት እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

ከዚህ በፊት የታክሲ ተራ አስከባሪ በመባል የሚታወቀውን አደረጃጀት በአዲስ መልክ በተደራጀው የተርሚናል ኢንተርፕራይዝ አማካኝነት የተሻለ የትራንስፖርት አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑን አንስተዋል።

በተርሚናል ኢንተርፕራይዝ የተደራጁ አስተባባሪዎችም የትራፊክ መጨናነቅና የተሳፋሪዎችን እንግልት በመቀነስ የተሳለጠ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ በመፍጠር ጉልህ ፋይዳ እያበረከቱ መሆኑን ገልጸዋል።

በአዲሱ የትራንስፖርት አስተባባሪዎች የተርሚናል ኢንተርፕራይዝም ግልጽና የአሰራር ሥርዓትን በተከተለ አግባብ በ87 ማኅበራት በማደራጀት የተሻለ አገልግሎት የሚሰጡበት ሁኔታ መፈጠሩን አስረድተዋል።

በአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ አማካኝነት በአዲስ በተዋቀረው የተርሚናል ኢንተርፕራይዝ የተደራጁ አስተባባሪዎችም የክህሎት ስልጠና ተሰጥቷቸው ወደስራ እንዲሰማሩ መደረጉን ገልጸው፤ የሚሰበስቡት ገንዘብ ዘመናዊ የአሰራር ሥርዓትን የተከተለ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢንተርፕራይዝ ማኅበራት አባላቱም ለሁለት ዓመታት በሚኖራቸው ቆይታ ዕድገት ተኮር በሆኑ ዘርፎች የሚሸጋገሩበት የቁጠባ ሥርዓት መዘርጋቱን አብራርተዋል።

በመዲናዋ የተደራጁ የተርሚናል ኢንተርፕራይዝ ማኅበራትም የነዋሪዎችን የትራንስፖርት አገልግሎት በማሳለጥ ምቹ የትራፊክ ፍሰት በመፍጠር አዎንታዊ ሚና እየተወጡ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.