የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በምዕራብ ሸዋ ዞን በ7 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ አትክልትና ፍራፍሬ እየለማ ነው

Oct 11, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አምቦ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን በ7 ሺህ 437 ሄክታር መሬት ላይ አትክልትና ፍራፍሬ እየለማ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ።

የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ባለሙያ አቶ መንገዱ ጉርሙ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዞኑ ለአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ትኩረት ተሰጥቶ ስራው እየተከናወነ ይገኛል።


በክረምቱ ወራትም በተከናወነ የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ስራ የተሻለ ምርት ለማግኘት የሰብል እንክብካቤ እና ጥበቃ እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።

በዚህ ወቅትም በ7 ሺህ 437 ሄክታር መሬት ላይ ምርጥ የአቮካዶ ዝርያዎች፣ ማንጎ፣ አፕል፣ ፓፓያና ሙዝ እየለማ መሆኑን ገልጸዋል።

በተጨማሪም ብርቱካን፣ ሎሚና ዘይቱን እንዲሁም ሌሎች የአትክልት አይነቶች እየለሙ መሆኑን ጠቅሰው በአጠቃላይ በአትክልትና ፍራፍሬዎች እየለማ ከሚገኘው መሬት 646 ሺህ ኩንታል ምርት ለማግኘት መታቀዱን ተናግረዋል።


የታቀደውን ምርት ለማግኘት የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ከወረዳ እስከ ቀበሌ ድረስ የግብርና ባለሙያዎችን መድቦ ድጋፍ እያደረገ መሆኑን አውስተዋል።

በአትክልትና ፍራፍሬ እየለማ ከሚገኘው መሬት ውስጥ አንድ ሺህ 353 ሔክታር መሬት በኩታ ገጠም የለማ መሆኑን ገልጸዋል።


አትክልትና ፍራፍሬ በብዛት እየለማ ያለባቸው ወረዳዎች ዳኖ፣ ኖኖ፣ ቶኬ ኩታዬ፣ ምዳቀኝ፣ ግንደበረት፣ ሊባን ጃዊ እና ጅባት ወረዳዎች እንደሆኑም ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.