🔇Unmute
አምቦ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን በ7 ሺህ 437 ሄክታር መሬት ላይ አትክልትና ፍራፍሬ እየለማ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ።
የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ባለሙያ አቶ መንገዱ ጉርሙ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዞኑ ለአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ትኩረት ተሰጥቶ ስራው እየተከናወነ ይገኛል።

በክረምቱ ወራትም በተከናወነ የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ስራ የተሻለ ምርት ለማግኘት የሰብል እንክብካቤ እና ጥበቃ እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።
በዚህ ወቅትም በ7 ሺህ 437 ሄክታር መሬት ላይ ምርጥ የአቮካዶ ዝርያዎች፣ ማንጎ፣ አፕል፣ ፓፓያና ሙዝ እየለማ መሆኑን ገልጸዋል።
በተጨማሪም ብርቱካን፣ ሎሚና ዘይቱን እንዲሁም ሌሎች የአትክልት አይነቶች እየለሙ መሆኑን ጠቅሰው በአጠቃላይ በአትክልትና ፍራፍሬዎች እየለማ ከሚገኘው መሬት 646 ሺህ ኩንታል ምርት ለማግኘት መታቀዱን ተናግረዋል።

የታቀደውን ምርት ለማግኘት የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ከወረዳ እስከ ቀበሌ ድረስ የግብርና ባለሙያዎችን መድቦ ድጋፍ እያደረገ መሆኑን አውስተዋል።
በአትክልትና ፍራፍሬ እየለማ ከሚገኘው መሬት ውስጥ አንድ ሺህ 353 ሔክታር መሬት በኩታ ገጠም የለማ መሆኑን ገልጸዋል።

አትክልትና ፍራፍሬ በብዛት እየለማ ያለባቸው ወረዳዎች ዳኖ፣ ኖኖ፣ ቶኬ ኩታዬ፣ ምዳቀኝ፣ ግንደበረት፣ ሊባን ጃዊ እና ጅባት ወረዳዎች እንደሆኑም ገልጸዋል፡፡
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026