🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 6/2018 (ኢዜአ)፡- በማኅበራዊ የመገናኛ መተግበሪያዎች አማካኝነት የማጭበርበር ወንጀሎች ፈጽመዋል የተባሉ አካላት በሕግ እንዲጠየቁ እየሠራ መሆኑን የፋይናንስ ደኅንነት አገልግሎት አስታወቀ።
አንዳንድ በማጭበርበር ድርጊት ላይ የተሰማሩ ሰዎች ከግለሰቦች ዕውቅና እና ፈቃድ ውጭ በሞባይሎቻቸው ውስጥ በመግባት የግለሰቦቹን የማኅበራዊ መገናኛ መተግበሪያዎች (እንደ ዋትስአፕ እና ቴሌግራም የመሳሰሉትን) ምስጢራዊ መረጃዎች በመስረቅ የገንዘብ ማጭበርበር ድርጊት ላይ መሰማራታቸውን አገልግሎቱ ገልጿል።
ግለሰቦቹ የማኅበራዊ መገናኛ መተግበሪያዎችን ከተቆጣጠሩ በኋላ እውነተኛ የአካውንት ባለቤት በመምሰል በግለሰቦቹ ስልኮች ተመዝግበው ለሚገኙ ቤተሰቦች፣ ዘመዶች፣ ጓደኞች፣ እና የሥራ ባልደረቦች ገንዘብ እንደተቸገሩ የሚገልፅ የጽሑፍ መልዕክት በመላክ ለዚሁ የማጭበርበር ዓላማ ወደ ተዘጋጀ የባንክ አካውንት እንዲላክላቸው ያደርጋሉ ብሏል፡፡
የፋይናንስ ደኅንነት አገልግሎት የደረሱትን ጥቆማዎችን መሰረት በማድረግ በወንጀል ድርጊቱ ላይ የተሳተፉ አካላትን በመለየት እና በመከታተል በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ከሚመለከታቸው ባለ ድርሻ ተቋማት ጋር በቅንጅት እየሠራ መሆኑን ለኢዜአ በላከው መረጃ አስታውቋል።
ሕብረተሰቡም ይህን የማጭበርበር ድርጊት ለመከላከል ወደ ስልኩ ለሚደርሱ መልዕክቶች ምላሽ ከመስጠቱ አስቀድሞ በተለያዩ መንገዶች የመልዕክቱን ትክክለኛነት በማረጋገጥ ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ አሳስቧል።
እንዲሁም ከሚመለከታቸው ተቋማት የሚተላለፉ የጥንቃቄ መልዕክቶችን በመከታተል ራሱን ከወንጀል ድርጊቶች እንዲጠብቅ እና ወንጀል ተፈፅሞ ሲገኝም ለሕግ አስከባሪ አካላት እንዲያሳውቅ ጥሪ አቅርቧል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025