🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ባለፉት ሦስት ወራት በቂ የግብርናና ኢንዱስትሪ ምርቶች እንዲቀርቡ በማድረግ ገበያውን ማረጋጋት መቻሉን አስታወቀ።
የግብርናው ዘርፍ ምርታማነት እንዲያድግ መንግሥት ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ያለው ሥራ በቂ አቅርቦት እንዲኖር ማስቻሉን እና የገበያ ዋጋን በማረጋጋት ሂደት በጎ ሚና ማበርከቱን በሚኒስቴሩ የሀገር ውስጥ ንግድ መሪ ሥራ አስፈጻሚ ሊቁ በነበሩ ተናግረዋል።
እንዲሁም መንግሥት በማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት ባንኮች ለዘርፉ ተዋንያኖች በቂ ምንዛሪ በማቅረባቸው ስኳርና የምግብ ዘይት በስፋት ለገበያ እንዲቀርብ አስችሏል ብለዋል።
በዚሁ መሠረት 1 ሚሊየን 677 ሺህ 934 ኩንታል ስኳር እና 198 ሚሊየን 949 ሺህ 288 ሊትር የምግብ ዘይት በነፃ ገበያው በኩል ለሸማቹ መቅረቡን ለኢዜአ ተናግረዋል።
በተጨማሪም 311 ሺህ ኩንታል ስኳርና 2 ሚሊየን ሊትር ዘይት በመንግሥት የልማት ድርጅቶች አማካኝነት ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው የሕብረተሰብ ክፍሎች በተመጣጣኝ ዋጋ መሠራጨቱን ነው ያረጋገጡት።
በቀጣይም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት የምርት አቅርቦትን በማሳደግ ገበያውን የማረጋጋቱ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አመላክተዋል።
በሌላ በኩል የቅዳሜና እሁድ ገበያዎችን ለማስፋት በተከናወነ ሥራ 71 አዳዲስ ገበያዎች መከፈታቸውን ጠቅሰው፤እስካሁንም 1 ሺህ 638 የሰንበት ገበያዎች አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን አስታውቀዋል።
በእነዚህ ገበያዎች በተፈጠረ የገበያ ትስስርም 1 ሚሊየን 86 ሺህ 419 ኩንታል የኢንዱስትሪ፣ 6 ሚሊየን 219 ሺህ 77 ኩንታል አትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም 2 ሚሊየን 93 ሺህ 120 ኩንታል የሰብል ምርቶች ግብይት መፈጸሙን ጠቁመዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026