🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 18/2018 (ኢዜአ)፡-የኮሪደር ልማት ሥራችን ከፍተኛ የፈጠራ ዐቅም እና የኑሮ ዘዬ ለውጥ እያመጣ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች እና አስተያየቶች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ከኮሪደር ልማት ጋር በተያያዘ በሰጡት ማብራሪያም፤ ከፍተኛ የአመለካከት ለውጥ የመጣበት ሥራ መሆኑን በአጽንኦት ገልጸዋል።
ሰው ከልማዱ ጋር ለመፋታት ቢቸገርም በሂደት አዲሱን ዓለም ይቀበላል፤ ስለዚህ ሥራችንን እናጠናክራለን ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የኮሪደር ልማት ሥራችን ከፍተኛ የፈጠራ ዐቅም እና የኑሮ ዘዬ ለውጥ እያመጣ ነው ብለዋል።
የኮሪደር ልማት ሥራው ብዙ ዐቅሞች እንዲወጡ ማስቻሉን ጠቁመው፤ለምሳሌ ከወንዝ ዳርቻዎች ልማት ጋር በተያያዘ የውጭ ሰዎች ከብዷቸው የተውትን የሀገራችን ሰዎች በብቃት እየሠሩት መሆኑን በአድናቆት አንስተዋል።
ከስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራ ሥራ ጋር በተያያዘም በአዲስ አበባ ብቻ ከ1 ሺህ በላይ አነስተኛ ስታዲየሞች ገንብተናል ብለዋል።
ይህ ማለትም ወጣቶችን ከጫት እና ከሽሻ ላይ ተሻምተን ወደ ኳስ ሜዳ እያስገባናቸው ነው ማለት ነው ሲሉ አብራርተዋል።
ዜጎችን ከድራፍት ቤት ተሻምተን ወደ ኳስ ሜዳ እያስገባን ነው፤በጋራ የእግር እንቅስቃሴ በማድረግ የቤተሰብ ቁርኝት እንዲያድግ አስችለናል።
የሚታይ ከተማ እየፈጠርን ነው፤እግር ኳስ ሜዳዎቹ በመጪዎቹ 10 ዓመታት ለብሔራዊ ቡድን ቁልፍ ተጫዋቾችን ለማፍራት ያግዛሉ።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026