🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 18/2018 (ኢዜአ)፡-የኮሪደር ልማት ሥራችን ከፍተኛ የፈጠራ ዐቅም እና የኑሮ ዘዬ ለውጥ እያመጣ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች እና አስተያየቶች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ከኮሪደር ልማት ጋር በተያያዘ በሰጡት ማብራሪያም፤ ከፍተኛ የአመለካከት ለውጥ የመጣበት ሥራ መሆኑን በአጽንኦት ገልጸዋል።
ሰው ከልማዱ ጋር ለመፋታት ቢቸገርም በሂደት አዲሱን ዓለም ይቀበላል፤ ስለዚህ ሥራችንን እናጠናክራለን ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የኮሪደር ልማት ሥራችን ከፍተኛ የፈጠራ ዐቅም እና የኑሮ ዘዬ ለውጥ እያመጣ ነው ብለዋል።
የኮሪደር ልማት ሥራው ብዙ ዐቅሞች እንዲወጡ ማስቻሉን ጠቁመው፤ለምሳሌ ከወንዝ ዳርቻዎች ልማት ጋር በተያያዘ የውጭ ሰዎች ከብዷቸው የተውትን የሀገራችን ሰዎች በብቃት እየሠሩት መሆኑን በአድናቆት አንስተዋል።
ከስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራ ሥራ ጋር በተያያዘም በአዲስ አበባ ብቻ ከ1 ሺህ በላይ አነስተኛ ስታዲየሞች ገንብተናል ብለዋል።
ይህ ማለትም ወጣቶችን ከጫት እና ከሽሻ ላይ ተሻምተን ወደ ኳስ ሜዳ እያስገባናቸው ነው ማለት ነው ሲሉ አብራርተዋል።
ዜጎችን ከድራፍት ቤት ተሻምተን ወደ ኳስ ሜዳ እያስገባን ነው፤በጋራ የእግር እንቅስቃሴ በማድረግ የቤተሰብ ቁርኝት እንዲያድግ አስችለናል።
የሚታይ ከተማ እየፈጠርን ነው፤እግር ኳስ ሜዳዎቹ በመጪዎቹ 10 ዓመታት ለብሔራዊ ቡድን ቁልፍ ተጫዋቾችን ለማፍራት ያግዛሉ።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026