🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 18/2018 (ኢዜአ)፡-የኮሪደር ልማት ሥራችን ከፍተኛ የፈጠራ ዐቅም እና የኑሮ ዘዬ ለውጥ እያመጣ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች እና አስተያየቶች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ከኮሪደር ልማት ጋር በተያያዘ በሰጡት ማብራሪያም፤ ከፍተኛ የአመለካከት ለውጥ የመጣበት ሥራ መሆኑን በአጽንኦት ገልጸዋል።
ሰው ከልማዱ ጋር ለመፋታት ቢቸገርም በሂደት አዲሱን ዓለም ይቀበላል፤ ስለዚህ ሥራችንን እናጠናክራለን ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የኮሪደር ልማት ሥራችን ከፍተኛ የፈጠራ ዐቅም እና የኑሮ ዘዬ ለውጥ እያመጣ ነው ብለዋል።
የኮሪደር ልማት ሥራው ብዙ ዐቅሞች እንዲወጡ ማስቻሉን ጠቁመው፤ለምሳሌ ከወንዝ ዳርቻዎች ልማት ጋር በተያያዘ የውጭ ሰዎች ከብዷቸው የተውትን የሀገራችን ሰዎች በብቃት እየሠሩት መሆኑን በአድናቆት አንስተዋል።
ከስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራ ሥራ ጋር በተያያዘም በአዲስ አበባ ብቻ ከ1 ሺህ በላይ አነስተኛ ስታዲየሞች ገንብተናል ብለዋል።
ይህ ማለትም ወጣቶችን ከጫት እና ከሽሻ ላይ ተሻምተን ወደ ኳስ ሜዳ እያስገባናቸው ነው ማለት ነው ሲሉ አብራርተዋል።
ዜጎችን ከድራፍት ቤት ተሻምተን ወደ ኳስ ሜዳ እያስገባን ነው፤በጋራ የእግር እንቅስቃሴ በማድረግ የቤተሰብ ቁርኝት እንዲያድግ አስችለናል።
የሚታይ ከተማ እየፈጠርን ነው፤እግር ኳስ ሜዳዎቹ በመጪዎቹ 10 ዓመታት ለብሔራዊ ቡድን ቁልፍ ተጫዋቾችን ለማፍራት ያግዛሉ።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025