የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

ትግራይ ልማት ያስፈልጋታል በመሆኑም በሰላማዊ መንገድ በትብብር ለልማት መስራት ይገባል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

Oct 29, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦ ትግራይ ልማት ያስፈልጋታል በመሆኑም በሰላማዊ መንገድ በትብብር ለልማት መስራት ይገባል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አስገነዘቡ።

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ እየተካሄደ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ይገኛሉ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በትግራይ ክልል ያለውን የሰላም ሁኔታ በሚመለከት በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ ትግራይ ልማት ያስፈልጋታል በመሆኑም በሰላማዊ መንገድ በትብብር ለልማት መስራት ይገባል ብለዋል።

በትግራይ ክልል ተጨማሪ ወጊያ እንዲካሄድ አንፈልግም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከዚያ ይልቅ ተባብረን ሀገር ማልማት ነው የምንፈልገው ነው ያሉት።

ከዚያ ውጭ መንግስትን በሃይል ለመጣል ፍላጎት ካለ እሱ ፈጽሞ ሊሳካ አይችልም የፌደራል መንግስት ለትግራይ ክልል የሚመድበው በጀት ለልማት ሳይሆን ለታጣቂ እየዋለ ነው ሲሉም ገልጸዋል።

ይህ ትክክል እንዳልሆነ ጠቁመውም ትግራይ ልማት ያስፈልጋታል በመሆኑም በሰላማዊ መንገድ በትብብር ለልማት መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.