🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦ ትግራይ ልማት ያስፈልጋታል በመሆኑም በሰላማዊ መንገድ በትብብር ለልማት መስራት ይገባል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አስገነዘቡ።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ እየተካሄደ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ይገኛሉ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በትግራይ ክልል ያለውን የሰላም ሁኔታ በሚመለከት በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ ትግራይ ልማት ያስፈልጋታል በመሆኑም በሰላማዊ መንገድ በትብብር ለልማት መስራት ይገባል ብለዋል።
በትግራይ ክልል ተጨማሪ ወጊያ እንዲካሄድ አንፈልግም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከዚያ ይልቅ ተባብረን ሀገር ማልማት ነው የምንፈልገው ነው ያሉት።
ከዚያ ውጭ መንግስትን በሃይል ለመጣል ፍላጎት ካለ እሱ ፈጽሞ ሊሳካ አይችልም የፌደራል መንግስት ለትግራይ ክልል የሚመድበው በጀት ለልማት ሳይሆን ለታጣቂ እየዋለ ነው ሲሉም ገልጸዋል።
ይህ ትክክል እንዳልሆነ ጠቁመውም ትግራይ ልማት ያስፈልጋታል በመሆኑም በሰላማዊ መንገድ በትብብር ለልማት መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026