የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በጠቅላይ ሚኒስትሩ ይፋ የተደረጉ የጉባ ላይ ብስራቶች ኢትዮጵያን በአፍሪካ የግዙፍ ኢኮኖሚ ባለቤት የሚያደርጉ ናቸው

Oct 31, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አሶሳ፤ ጥቅምት 20/2018(ኢዜአ)፦ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ይፋ የተደረጉ የጉባ ላይ ብስራቶች ኢትዮጵያን በአፍሪካ የግዙፍ ኢኮኖሚ ባለቤት የሚያደርጉ መሆናቸውን በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ የምጣኔ ሃብት መምህርና ተመራማሪው ሙሐመድ ኢብራሂም ተናገሩ።

በአፍሪካ ግዙፍ የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከ14 ዓመታት የግንባታ ሂደት በኋላ ተጠናቆ በይፋ ተመርቆ ለአገለግሎት መብቃቱ ይታወቃል።

የዚህ ግድብ መጠናቀቅ በቀጣናው የኃይል ትስስር ለመፍጠርና የኢትዮጵያን ማንሰራራት እውን የሚያደረግ ስለመሆኑም ተነስቷል።

በመሆኑም የህዳሴ ግድብ መጠናቀቅን ተከትሎ የኢትዮጵያን እድገትና ማንሰራራት ዘላቂ ለማድረግና የሀገሪቷን የወደፊት እጣ ፋንታ የሚወስኑ የተለያዩ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ግንባታ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጉባ ላይ ይፋ መደረጋቸው ይታወሳል።

በጠቅላይ ሚኒስትሩ ይፋ የተደረጉት የጉባ ላይ ብስራቶች ምን ትርጉም አላቸው ሲል ኢዜአ በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ የምጣኔ ሃብት መምህርና ተመራማሪ የሆኑትን ሙሐመድ ኢብራሂምን አነጋግሯል።

መምህሩ በማብራሪያቸው የመንግስት የልማት ጥረቶች በሀገር ላይ መሰረታዊ ለውጦችን ማምጣት የሚችሉ እና የኢትዮጵያን ማንሰራራት የሚያስቀጥሉ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የጉባ ላይ ብስራቶች ኢትዮጵያን በአፍሪካ የግዙፍ ኢኮኖሚ ባለቤት የሚያደርጉ የእድገትና ብልጽግና ማረጋገጫ ሁነኛ መገለጫዎች ናቸው ሲሉም አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ከግብርና መር ተላቆ ብዝሃ ዘርፎችን ማእከል አድርጎ እየተሰራበት በመሆኑ መሰረታዊ ለውጥ እየታየበት መሆኑንም አንስተዋል።

ከዚህ በተጨማሪ በሀገሪቷ የተከናወኑ እና በሂደት ላይ ያሉ እንዲሁም በእቅድ የተያዙ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች የኢትዮጵያን የወደፊት እጣ ፈንታ የሚወስኑ ናቸው ብለዋል።

በኢትዮጵያ የፕሮጀክቶች ግንባታ ሂደት ፍጥነትን፣ ጥራትንና ብቃትን አጣምሮ የመፈፀም አቅም በተግባር እየታየ በመሆኑ የሚፈለገው ሀገራዊ ስኬት እድገትና ብልጽግና እውን የሚሆንበት ጊዜ ብዙም ሩቅ ሊሆን እንደማይችል ተናግረዋል።

በጠቅላይ ሚኒስትሩ ይፋ የተደረጉት የጉባ ላይ ብስራቶች የማዳበሪያ ፋብሪካ፣ የኒውክሌር ግንባታ ፕላንት፣ ግዙፉ የቢሾፍቱ አውሮፕላን ማረፊያ፣ የ1 ነጥብ 5 ሚሊየን ቤቶች ግንባታና የጋዝ ልማትን ጨምሮ በድምሩ የ30 ቢሊዮን ብር ፕሮጀክቶች መሆናቸው ይታወቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.