🔇Unmute
አሶሳ፤ ጥቅምት 20/2018(ኢዜአ)፦ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ይፋ የተደረጉ የጉባ ላይ ብስራቶች ኢትዮጵያን በአፍሪካ የግዙፍ ኢኮኖሚ ባለቤት የሚያደርጉ መሆናቸውን በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ የምጣኔ ሃብት መምህርና ተመራማሪው ሙሐመድ ኢብራሂም ተናገሩ።
በአፍሪካ ግዙፍ የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከ14 ዓመታት የግንባታ ሂደት በኋላ ተጠናቆ በይፋ ተመርቆ ለአገለግሎት መብቃቱ ይታወቃል።
የዚህ ግድብ መጠናቀቅ በቀጣናው የኃይል ትስስር ለመፍጠርና የኢትዮጵያን ማንሰራራት እውን የሚያደረግ ስለመሆኑም ተነስቷል።
በመሆኑም የህዳሴ ግድብ መጠናቀቅን ተከትሎ የኢትዮጵያን እድገትና ማንሰራራት ዘላቂ ለማድረግና የሀገሪቷን የወደፊት እጣ ፋንታ የሚወስኑ የተለያዩ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ግንባታ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጉባ ላይ ይፋ መደረጋቸው ይታወሳል።
በጠቅላይ ሚኒስትሩ ይፋ የተደረጉት የጉባ ላይ ብስራቶች ምን ትርጉም አላቸው ሲል ኢዜአ በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ የምጣኔ ሃብት መምህርና ተመራማሪ የሆኑትን ሙሐመድ ኢብራሂምን አነጋግሯል።
መምህሩ በማብራሪያቸው የመንግስት የልማት ጥረቶች በሀገር ላይ መሰረታዊ ለውጦችን ማምጣት የሚችሉ እና የኢትዮጵያን ማንሰራራት የሚያስቀጥሉ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የጉባ ላይ ብስራቶች ኢትዮጵያን በአፍሪካ የግዙፍ ኢኮኖሚ ባለቤት የሚያደርጉ የእድገትና ብልጽግና ማረጋገጫ ሁነኛ መገለጫዎች ናቸው ሲሉም አብራርተዋል።
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ከግብርና መር ተላቆ ብዝሃ ዘርፎችን ማእከል አድርጎ እየተሰራበት በመሆኑ መሰረታዊ ለውጥ እየታየበት መሆኑንም አንስተዋል።
ከዚህ በተጨማሪ በሀገሪቷ የተከናወኑ እና በሂደት ላይ ያሉ እንዲሁም በእቅድ የተያዙ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች የኢትዮጵያን የወደፊት እጣ ፈንታ የሚወስኑ ናቸው ብለዋል።
በኢትዮጵያ የፕሮጀክቶች ግንባታ ሂደት ፍጥነትን፣ ጥራትንና ብቃትን አጣምሮ የመፈፀም አቅም በተግባር እየታየ በመሆኑ የሚፈለገው ሀገራዊ ስኬት እድገትና ብልጽግና እውን የሚሆንበት ጊዜ ብዙም ሩቅ ሊሆን እንደማይችል ተናግረዋል።
በጠቅላይ ሚኒስትሩ ይፋ የተደረጉት የጉባ ላይ ብስራቶች የማዳበሪያ ፋብሪካ፣ የኒውክሌር ግንባታ ፕላንት፣ ግዙፉ የቢሾፍቱ አውሮፕላን ማረፊያ፣ የ1 ነጥብ 5 ሚሊየን ቤቶች ግንባታና የጋዝ ልማትን ጨምሮ በድምሩ የ30 ቢሊዮን ብር ፕሮጀክቶች መሆናቸው ይታወቃል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026