🔇Unmute
አሶሳ፤ ጥቅምት 20/2018(ኢዜአ)፦ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ይፋ የተደረጉ የጉባ ላይ ብስራቶች ኢትዮጵያን በአፍሪካ የግዙፍ ኢኮኖሚ ባለቤት የሚያደርጉ መሆናቸውን በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ የምጣኔ ሃብት መምህርና ተመራማሪው ሙሐመድ ኢብራሂም ተናገሩ።
በአፍሪካ ግዙፍ የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከ14 ዓመታት የግንባታ ሂደት በኋላ ተጠናቆ በይፋ ተመርቆ ለአገለግሎት መብቃቱ ይታወቃል።
የዚህ ግድብ መጠናቀቅ በቀጣናው የኃይል ትስስር ለመፍጠርና የኢትዮጵያን ማንሰራራት እውን የሚያደረግ ስለመሆኑም ተነስቷል።
በመሆኑም የህዳሴ ግድብ መጠናቀቅን ተከትሎ የኢትዮጵያን እድገትና ማንሰራራት ዘላቂ ለማድረግና የሀገሪቷን የወደፊት እጣ ፋንታ የሚወስኑ የተለያዩ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ግንባታ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጉባ ላይ ይፋ መደረጋቸው ይታወሳል።
በጠቅላይ ሚኒስትሩ ይፋ የተደረጉት የጉባ ላይ ብስራቶች ምን ትርጉም አላቸው ሲል ኢዜአ በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ የምጣኔ ሃብት መምህርና ተመራማሪ የሆኑትን ሙሐመድ ኢብራሂምን አነጋግሯል።
መምህሩ በማብራሪያቸው የመንግስት የልማት ጥረቶች በሀገር ላይ መሰረታዊ ለውጦችን ማምጣት የሚችሉ እና የኢትዮጵያን ማንሰራራት የሚያስቀጥሉ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የጉባ ላይ ብስራቶች ኢትዮጵያን በአፍሪካ የግዙፍ ኢኮኖሚ ባለቤት የሚያደርጉ የእድገትና ብልጽግና ማረጋገጫ ሁነኛ መገለጫዎች ናቸው ሲሉም አብራርተዋል።
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ከግብርና መር ተላቆ ብዝሃ ዘርፎችን ማእከል አድርጎ እየተሰራበት በመሆኑ መሰረታዊ ለውጥ እየታየበት መሆኑንም አንስተዋል።
ከዚህ በተጨማሪ በሀገሪቷ የተከናወኑ እና በሂደት ላይ ያሉ እንዲሁም በእቅድ የተያዙ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች የኢትዮጵያን የወደፊት እጣ ፈንታ የሚወስኑ ናቸው ብለዋል።
በኢትዮጵያ የፕሮጀክቶች ግንባታ ሂደት ፍጥነትን፣ ጥራትንና ብቃትን አጣምሮ የመፈፀም አቅም በተግባር እየታየ በመሆኑ የሚፈለገው ሀገራዊ ስኬት እድገትና ብልጽግና እውን የሚሆንበት ጊዜ ብዙም ሩቅ ሊሆን እንደማይችል ተናግረዋል።
በጠቅላይ ሚኒስትሩ ይፋ የተደረጉት የጉባ ላይ ብስራቶች የማዳበሪያ ፋብሪካ፣ የኒውክሌር ግንባታ ፕላንት፣ ግዙፉ የቢሾፍቱ አውሮፕላን ማረፊያ፣ የ1 ነጥብ 5 ሚሊየን ቤቶች ግንባታና የጋዝ ልማትን ጨምሮ በድምሩ የ30 ቢሊዮን ብር ፕሮጀክቶች መሆናቸው ይታወቃል።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026