🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 26/2018(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት የድርድር አባልነት ድርድር አካል የሆነውንና ሦስተኛውን የሁለትዮሽ የገበያ ድርድር ከቻይና ጋር በማጠናቀቅ በጄኔቫ ተፈራርማለች።
ፊርማውን በተባበሩት መንግሥታት እና ጄኔቫ በሚገኙ ሌሎች ዓለም አቀፍ ድርጅቶች የኢትዮጵያ አምባሳደር እና ቋሚ ተወካይ አምባሳደር ፀጋአብ ክበበውና በዓለም ንግድ ድርጅት የቻይና አምባሳደር እና ቋሚ ተወካይ ሊ ዮንግጂ ፈርመውታል።
እዚህ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የተደረሰው ሀገራቱ መካከል ውጤታማ ውይይቶችና ቴክኒካል ድርድሮች ከተደረጉ በኋላ መሆኑም ተጠቁሟል።
ይህም የኢኮኖሚ ትብብርን ለማጠናከር፣ ፍትሐዊ፣ ሁሉን አቀፍ እና ሕጎችን መሠረት ያደረገ ዓለም አቀፍ የንግድ ሥርዓትን ለማንበር ያላቸውን ቁርጠኝነት ያሳያል ተብሏል።
የዓለም ንግድ ድርጅት የድርድር አባልነት ድርድር አካል የሆነውን ይህን የሁለትዮሽ የገበያ ድርድር ኢትዮጵያ ቀደም ሲል ከቱርክዬ እና አርጀንቲና ጋር መፈራረሟ ይታወቃል።
በቀጣይም ከሌሎች ሀገራት ጋር ተመሳሳይ ድርድሮችን በማጠናቀቅ መፈራረም የሚያስችሉ ሥራዎች በትኩረት እየተከናወኑ ይገኛሉ።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ...
Feb 8, 2025