🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 26/2018(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት የድርድር አባልነት ድርድር አካል የሆነውንና ሦስተኛውን የሁለትዮሽ የገበያ ድርድር ከቻይና ጋር በማጠናቀቅ በጄኔቫ ተፈራርማለች።
ፊርማውን በተባበሩት መንግሥታት እና ጄኔቫ በሚገኙ ሌሎች ዓለም አቀፍ ድርጅቶች የኢትዮጵያ አምባሳደር እና ቋሚ ተወካይ አምባሳደር ፀጋአብ ክበበውና በዓለም ንግድ ድርጅት የቻይና አምባሳደር እና ቋሚ ተወካይ ሊ ዮንግጂ ፈርመውታል።
እዚህ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የተደረሰው ሀገራቱ መካከል ውጤታማ ውይይቶችና ቴክኒካል ድርድሮች ከተደረጉ በኋላ መሆኑም ተጠቁሟል።
ይህም የኢኮኖሚ ትብብርን ለማጠናከር፣ ፍትሐዊ፣ ሁሉን አቀፍ እና ሕጎችን መሠረት ያደረገ ዓለም አቀፍ የንግድ ሥርዓትን ለማንበር ያላቸውን ቁርጠኝነት ያሳያል ተብሏል።
የዓለም ንግድ ድርጅት የድርድር አባልነት ድርድር አካል የሆነውን ይህን የሁለትዮሽ የገበያ ድርድር ኢትዮጵያ ቀደም ሲል ከቱርክዬ እና አርጀንቲና ጋር መፈራረሟ ይታወቃል።
በቀጣይም ከሌሎች ሀገራት ጋር ተመሳሳይ ድርድሮችን በማጠናቀቅ መፈራረም የሚያስችሉ ሥራዎች በትኩረት እየተከናወኑ ይገኛሉ።
ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
May 21, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026