🔇Unmute
ሆሳዕና ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፦ የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንድናገኝ አስችሎናል ሲሉ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሆሳዕና ማዕከል ተገልጋዮች ገለጹ፡፡
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ መሶብ የአንድ ማእከል አገልግሎት መስከረም 15 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ ሥራ መጀመሩ ይታወቃል።

የማዕከሉን የሥራ እንቅስቃሴ በተመለከተ የኢዜአ ሪፖርተር በስፍራው በመገኘት ተገልጋዮችና የሚመለከታቸውን የሥራ ሃላፊዎች አነጋግሯል።
ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል አቶ ዳንኤል በየነ፣ አቶ ደስታ ኤርቻዮ እና አቶ ደመቀ ሙሉነህ ፤ መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለማግኘት እንዳስቻላቸው ተናግረዋል።
አገልግሎቱ በአንድ ማዕከል በርካታ ጉዳዮችን ጨርሶ መውጣት ከማስቻሉ ባለፈ ፈጣን፣ ቀልጣፋ፣ ጊዜና ገንዘብ ቆጣቢ መሆኑንም ተናግረዋል።
በመሆኑም መሰል የአገልግሎት ማዕከላትን በማስፋት በተገልጋዮች ላይ ሲደርስ የነበረን እንግልት እና የብልሹ አሰራር መንስኤዎችን ማስቀረት አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል።

የማዕከሉ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ከበደ ሻሜቦ፤ በማዕከሉ የተለያዩ ተቋማት 20 አገልግሎቶች እየተሰጡ መሆኑን ገልጸው በቀጣይ በማዕከሉ የሚሰጡ አገልግሎቶች እየሰፋ ይሄዳሉ ብለዋል።
በማዕከሉ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ከመስጠት ባለፈ ብልሹ አሰራሮችን ለማስቀረት እያስቻለ በመሆኑ በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል ብለዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026