🔇Unmute
ሆሳዕና ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፦ የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንድናገኝ አስችሎናል ሲሉ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሆሳዕና ማዕከል ተገልጋዮች ገለጹ፡፡
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ መሶብ የአንድ ማእከል አገልግሎት መስከረም 15 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ ሥራ መጀመሩ ይታወቃል።

የማዕከሉን የሥራ እንቅስቃሴ በተመለከተ የኢዜአ ሪፖርተር በስፍራው በመገኘት ተገልጋዮችና የሚመለከታቸውን የሥራ ሃላፊዎች አነጋግሯል።
ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል አቶ ዳንኤል በየነ፣ አቶ ደስታ ኤርቻዮ እና አቶ ደመቀ ሙሉነህ ፤ መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለማግኘት እንዳስቻላቸው ተናግረዋል።
አገልግሎቱ በአንድ ማዕከል በርካታ ጉዳዮችን ጨርሶ መውጣት ከማስቻሉ ባለፈ ፈጣን፣ ቀልጣፋ፣ ጊዜና ገንዘብ ቆጣቢ መሆኑንም ተናግረዋል።
በመሆኑም መሰል የአገልግሎት ማዕከላትን በማስፋት በተገልጋዮች ላይ ሲደርስ የነበረን እንግልት እና የብልሹ አሰራር መንስኤዎችን ማስቀረት አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል።

የማዕከሉ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ከበደ ሻሜቦ፤ በማዕከሉ የተለያዩ ተቋማት 20 አገልግሎቶች እየተሰጡ መሆኑን ገልጸው በቀጣይ በማዕከሉ የሚሰጡ አገልግሎቶች እየሰፋ ይሄዳሉ ብለዋል።
በማዕከሉ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ከመስጠት ባለፈ ብልሹ አሰራሮችን ለማስቀረት እያስቻለ በመሆኑ በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል ብለዋል።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026