🔇Unmute
አምቦ ፤ ህዳር 3/2018 (ኢዜአ)፡-በምእራብ ሸዋ ዞን በዘንድሮ የበጋ ወራት 466 ሺህ 750 ሄክታር መሬት በመስኖ እየለማ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡
በጽህፈት ቤቱ የአትክልት ባለሙያ አቶ መላኩ ተፈራ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዞኑ የከርሰ ምድርና የገፀ ምድር የውሃ ሃብትን በመጠቀም የመስኖ ልማት ስራት በስፋት የማከናወን ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።

በመስኖ እና የግብርና ግብዓት አጠቃቀም እንዲሁም ሌሎች ተያያዥ ስራዎች ላይ ለአምራቾች ግንዛቤ በመስጠት ወደ ስራ እንዲገቡ መደረጉን ተናግረዋል።
በዚህም መሰረት በዘንድሮው ዓመት በዞኑ ከ400 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በመስኖ ለማልማት ታቅዶ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
በእስካሁኑ ሂደትም ከ70 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ስንዴን ጨምሮ በተለያዩ ሰብሎች ስለመሸፈኑ ጠቅሰው እቅዱን ለማሳካት የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህ ዓመት በሁለት ዙሮች ከሚካሄደው በበጋ መስኖ ልማት ከ26 ነጥብ5 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱንም ተናግረዋል፡፡
በዞኑ ባለፈው ዓመት በአንደኛና በሁለተኛ ዙር በመስኖ ከለማ መሬት 25 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱን ከጽህፈት ቤቱ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026