🔇Unmute
አምቦ ፤ ህዳር 3/2018 (ኢዜአ)፡-በምእራብ ሸዋ ዞን በዘንድሮ የበጋ ወራት 466 ሺህ 750 ሄክታር መሬት በመስኖ እየለማ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡
በጽህፈት ቤቱ የአትክልት ባለሙያ አቶ መላኩ ተፈራ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዞኑ የከርሰ ምድርና የገፀ ምድር የውሃ ሃብትን በመጠቀም የመስኖ ልማት ስራት በስፋት የማከናወን ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።

በመስኖ እና የግብርና ግብዓት አጠቃቀም እንዲሁም ሌሎች ተያያዥ ስራዎች ላይ ለአምራቾች ግንዛቤ በመስጠት ወደ ስራ እንዲገቡ መደረጉን ተናግረዋል።
በዚህም መሰረት በዘንድሮው ዓመት በዞኑ ከ400 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በመስኖ ለማልማት ታቅዶ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
በእስካሁኑ ሂደትም ከ70 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ስንዴን ጨምሮ በተለያዩ ሰብሎች ስለመሸፈኑ ጠቅሰው እቅዱን ለማሳካት የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህ ዓመት በሁለት ዙሮች ከሚካሄደው በበጋ መስኖ ልማት ከ26 ነጥብ5 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱንም ተናግረዋል፡፡
በዞኑ ባለፈው ዓመት በአንደኛና በሁለተኛ ዙር በመስኖ ከለማ መሬት 25 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱን ከጽህፈት ቤቱ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026