የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በክልሉ ባለፉት አራት ወራት ከ2 ሺህ 798 ኪሎ ግራም በላይ የተጣራ ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ገቢ ተደርጓል

Nov 21, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ጋምቤላ ፤ሕዳር 12/2018(ኢዜአ)፡-በጋምቤላ ክልል ባለፉት አራት ወራት ከ2 ሺህ 798 ኪሎ ግራም በላይ የተጣራ ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ገቢ መደረጉን የክልሉ ማዕድን ሀብት ልማት መስሪያ ቤት አስታወቀ።

በክልሉ ባለፉት አራት ወራት ለብሔራዊ ባንክ የገባው የወርቅ ምርት መጠን ከእቅዱ በ673 ኪሎ ግራም ብልጫ ያለው መሆኑን የማዕድን ልማት መስሪያ ቤቱ ገልጿል።


የጋምቤላ ክልል ማዕድን ሀብት ልማት መስሪያ ቤት ዋና ዳይሬክተር አቶ ኡጁሉ ጊሎ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ እንደ ሀገር ለብዝሃ ኢኮኖሚ ተብለው ተለይተው በልዩ ትኩረት እየተሰራባቸው ከሚገኙት ዘርፎች መካከል አንዱ የወርቅ ማዕድን ነው።

ይህን ታሳቢ በማድረግም በክልሉ ለወርቅ ማዕድን ልማቱ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝና በዘርፉም ስኬት እየተመዘገበ መሆኑን ገልጸዋል።


በክልሉ ባለፉት አራት ወራት በዘርፉ በተከናወኑት ስራዎች የህዳር ወር የመጀመሪያ ሳምንትን ጨምሮ ከ2 ሺህ 798 ኪሎ ግራም በላይ የተጣራ ወርቅ ለብሄራዊ ባንክ ገቢ ማድርግ ተችሏል ብለዋል።

ባለፈው አራት ወራት ለብሔራዊ ባንክ ገቢ የተደረገው የወርቅ መጠን ከእቅዱ በ673 ኪሎ ግራም ብልጫ ያለው ሲሆን ከቀዳሚው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር ደግሞ ከ1 ሺህ 420 ኪሎግራም በላይ ብልጫ ያለው መሆኑንም ተናግረዋል።

ባለፉት አራት ወራት ለብሄራዊ ባንክ የገባው ወርቅ በክልሉ በሚገኙ የዲማ፣ የአቦቦ፣ የጋምቤላና የመንገሺ ወረዳዎች በባህላዊ፣ ልዩ አነስተኛና በዘመናዊ ኩባንያዎች የተመረተ መሆኑን ገልጸዋል።


በክልሉ በተያዘው በጀት ዓመት አራት ወራት ውስጥ ከእቅድ በላይና ከቀዳሚ ዓመት የተሻለ የወርቅ ምርት ወደ ብሔራዊ ባንክ ሊገባ የቻለው በሀገር አቀፍ ደረጃ በተደረገው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያና በተጠናከረ የክትትልና ድጋፍ ስራ መሆኑን ተናግረዋል።

በቀጣይም የተጀመሩትን ስራዎች ይበልጥ በማጠናከር በበጀት ዓመቱ ለብሔራዊ ባንክ ከ6 ሺህ ኪሎ ግራም በላይ የተጣራ ወርቅ ለማስገባት የተያዘውን እቅድ ለማሳካት በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ዋና ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.