የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የተቀናጁ አሠራሮችን በመጠቀም በፓርኮች ላይ የሚደርስ ጉዳት መቀነስ ተችሏል

Nov 21, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሕዳር 12/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን በብሔራዊ ፓርኮችና የዱር እንስሳት መጠለያዎች እያከናወናቸው ያሉ አሠራሮች ሕገ ወጥ ድርጊቶች እንዲቀንሱ ማስቻላቸውን ገለጸ።

ባለሥልጣኑ በጀት መድቦ በቀጥታ በሥሩ የሚያስተዳድራቸው 11 ብሔራዊ ፓርኮች እና ሁለት የዱር እንስሳት መጠለያዎች መሆናቸውን አስታውቋል።


በክልሎች ሥር ለሚተዳደሩ ብሔራዊ ፓርኮችም የስልጠና፣ የቁሳቁስና መሰል ድጋፍ እንደሚያደርግ የባለሥልጣኑ የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ተወካይ ሥራ አስፈጻሚ ታምሩ መክት ለኢዜአ ተናግረዋል።

የብሔራዊ ፓርክና የዱር እንስሳት መጠለያ ጠባቂዎችን በማሰልጠን፣ ለጥበቃ የሚሆኑ ትጥቆችን በማቅረብ፣ በቂ የሰው ኃይል በማሟላት፣ ካሉበት ሆነው መረጃዎችን የሚለዋወጡበት በቴክኖሎጂ የታገዘ አሠራርን እንዲከተሉ ማድረግ መቻሉን አንስተዋል።

በየአካባቢዎቹ የሚገኙ ነዋሪዎች የኔ ነው ብለው በንቃት እንዲጠብቁ ግንዛቤ የማስጨበጥ ሥራ መከናወኑንም ጠቁመዋል።


ወጣቶች ተደራጅተው እንዲጠብቁ የማድረግ ሥራ መከናወኑን ጠቁመው፤ ባለሥልጣኑ እየሰራቸው ያሉ አሠራሮች ከሕብረተሰቡ ትብብር ጋር ተቀናጅተው ሕገ ወጥ ድርጊቶች እንዲቀንሱ ማስቻላቸውን ተናግረዋል።

ዓለም አቀፍ ወንጀል የሆነውን ሕገ ወጥ የዱር እንስሳት ውጤቶች ዝውውር ከመቆጣጠር አኳያም፤ በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በአነፍናፊ ውሻዎች ጭምር የቁጥጥር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

በአነፍናፊ ውሻዎች ታግዞ እየተሠራ ያለው የቁጥጥር ሥራ ውጤታማ መሆኑን አንስተው፤ በዚህም በሕገ ወጥ መንገድ የሚደረግ የእንስሳት ውጤቶች ዝውውር ቀንሷል ነው ያሉት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.