🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 12/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን በብሔራዊ ፓርኮችና የዱር እንስሳት መጠለያዎች እያከናወናቸው ያሉ አሠራሮች ሕገ ወጥ ድርጊቶች እንዲቀንሱ ማስቻላቸውን ገለጸ።
ባለሥልጣኑ በጀት መድቦ በቀጥታ በሥሩ የሚያስተዳድራቸው 11 ብሔራዊ ፓርኮች እና ሁለት የዱር እንስሳት መጠለያዎች መሆናቸውን አስታውቋል።

በክልሎች ሥር ለሚተዳደሩ ብሔራዊ ፓርኮችም የስልጠና፣ የቁሳቁስና መሰል ድጋፍ እንደሚያደርግ የባለሥልጣኑ የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ተወካይ ሥራ አስፈጻሚ ታምሩ መክት ለኢዜአ ተናግረዋል።
የብሔራዊ ፓርክና የዱር እንስሳት መጠለያ ጠባቂዎችን በማሰልጠን፣ ለጥበቃ የሚሆኑ ትጥቆችን በማቅረብ፣ በቂ የሰው ኃይል በማሟላት፣ ካሉበት ሆነው መረጃዎችን የሚለዋወጡበት በቴክኖሎጂ የታገዘ አሠራርን እንዲከተሉ ማድረግ መቻሉን አንስተዋል።
በየአካባቢዎቹ የሚገኙ ነዋሪዎች የኔ ነው ብለው በንቃት እንዲጠብቁ ግንዛቤ የማስጨበጥ ሥራ መከናወኑንም ጠቁመዋል።

ወጣቶች ተደራጅተው እንዲጠብቁ የማድረግ ሥራ መከናወኑን ጠቁመው፤ ባለሥልጣኑ እየሰራቸው ያሉ አሠራሮች ከሕብረተሰቡ ትብብር ጋር ተቀናጅተው ሕገ ወጥ ድርጊቶች እንዲቀንሱ ማስቻላቸውን ተናግረዋል።
ዓለም አቀፍ ወንጀል የሆነውን ሕገ ወጥ የዱር እንስሳት ውጤቶች ዝውውር ከመቆጣጠር አኳያም፤ በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በአነፍናፊ ውሻዎች ጭምር የቁጥጥር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
በአነፍናፊ ውሻዎች ታግዞ እየተሠራ ያለው የቁጥጥር ሥራ ውጤታማ መሆኑን አንስተው፤ በዚህም በሕገ ወጥ መንገድ የሚደረግ የእንስሳት ውጤቶች ዝውውር ቀንሷል ነው ያሉት።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026