የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በክልሉ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በማስፋፋት የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የባለድርሻ አካላት ድጋፍ ሊጠናከር ይገባል 

Jun 26, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጋምቤላ፤ ሰኔ 18/2018 (ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በማስፋፋት የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ለተያዘው ግብ መሳካት፣ የባለድርሻ አካላት ድጋፍና ትብብር ሊጠናከር እንደሚገባ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ዓለሚቱ ኡሞድ ገለጹ።

ርዕሰ መስተዳድሯን ጨምሮ የክልልና የፌደራል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ በአቦቦ ወረዳ በሩዝ ሰብል ላይ እየተካሄደ ያለውን የምርምር ሥራ ዛሬ ጎብኝተዋል።


ርዕሰ መስተዳድሯ በወቅቱ እንዳሉት፤ የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ የሚቻለው የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን ማስፋፋትና ተደራሽ ማድረግ ሲቻል ነው።

ክልሉ ያለውን ሰፊ የመሬትና የውኃ ሀብት በምርምር መደገፍ ከተቻለ፣ ለአካባቢው ብቻ ሳይሆን ለሀገር የሚተርፍ የሰብል ምርት ማግኘት እንደሚቻልም ተናግረዋል።

ጋምቤላ ለሁሉም የግብርና ልማት ዓይነቶች ምቹ ሥነ-ምህዳር ያላት መሆኑን የጠቀሱት ወይዘሮ ዓለሚቱ፤ በተለይም የሩዝ ሰብል አዋጭ ተብለው ከተለዩት የሰብል ዓይነቶች በቀዳሚነት የሚጠቀስ መሆኑን ገልጸዋል።

በክልሉ የሩዝ ልማትን ማዘመንና ማስፋፋት ከተቻለ ለአገር ውስጥ ፍጆታ አልፎ ለውጭ ገበያ የሚተርፍ ምርት ማግኘት እንደሚቻልም አክለዋል።


ልማቱን ለመደገፍ በባዮና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት፣ በጋምቤላ ዩኒቨርሲቲና በቻይናው ዩናን ዩኒቨርሲቲ ቅንጅት እየተካሄደ ያለው የምርምር ሥራ የሚበረታታ መሆኑን በመግለጽ፣ ለሥራው ስኬታማነት የክልሉ መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍና ትብብር እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።

በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት ልማት፣ የሥራ ስምሪትና የቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ እንደ ሀገር የታለመውን የግብርና ልማት ስኬታማ ማድረግ የሚቻለው አዳዲስ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በማፍለቅ ለአርሶ አደሩና ለባለሀብቱ ተደራሽ ማድረግ ሲቻል መሆኑን ገልጸዋል።

በመሆኑም በተለያዩ ተቋማት ትብብር በሩዝ ሰብል ላይ የተጀመረው የምርምር ሥራ ተስፋ ሰጪና ዘርፉን የሚያጠናክር መሆኑን ተናግረዋል።


የባዮና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር ካሳሁን ተስፋዬ በበኩላቸው፤ የምርምር ሥራው እየተካሄደ ያለው ከቻይናው ዩናን ዩኒቨርሲቲ ጋር መሆኑን አስረድተዋል።

የአዲሱ የሩዝ ዝርያ ልዩ ባህሪያት መካከል በአጭር ጊዜ ውስጥ የሚደርስ መሆኑ እንዲሁም በዓመት እስከ ሦስት ጊዜ መመረቱ እንደሆነ ገልጸዋል።

በሩዝ ዝርያዎቹ ላይ እየተካሄደ ያለው የማላመድ የምርምር ሥራ በሚቀጥለው ዓመት ተጠናቆ ለተጠቃሚዎች ተደራሽ እንደሚሆንም ዋና ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በማስፋፋት የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የባለድርሻ አካላት ድጋፍ ሊጠናከር ይገባል 

ጋምቤላ፤ ሰኔ 18/2018 (ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በማስፋፋት የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ለተያዘው ግብ መሳካት፣ የባለድ...

Jun 26, 2026

አዲሱ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ፣ ከአዲስ አበባ 40 ኪ.ሜ ርቀት ላይ፣ ከባሕር ጠለል በላይ በ1,910 ሜትር ከፍታ ላይ እየተገነባ ይገኛል

‎አዲስ አበባ፤ ሰኔ 8/2018 (ኢዜአ)፦አዲሱ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ፣ ከአዲስ አበባ 40 ኪ.ሜ ርቀት ላይ፣ ከባሕር ጠለል በላይ በ1,910 ...

Jun 16, 2026

በክልሉ ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ ነው-ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ

ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

May 21, 2026

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026