🔇Unmute
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መምጣቱን ተሳፋሪዎችና አሽከርካሪዎች ገለጹ።
የወላይታ ሶዶ ከተማ ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ መምሪያ በበኩሉ አገልግሎቱን ለማስተጓጎልና ህዝቡን ለማማረር በሚሰሩ አሽከርካሪዎች ላይ የሚደረገው ክትትልና ቁጥጥር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጿል።
ከወላይታ ሶዶ ከተማ ወደ ሻሸመኔ እና ሀዋሳ ከተሞች ሲጓዙ የነበሩት ወይዘሮ ብዙአየሁ ሊዮን እና ፓስተር ዳዊት ደግሰው የነዳጅ እጥረቱን ምክንያት በማድረግ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ሲገጥም የነበረው እንግልት መፈታቱን ተናግረዋል።
የትራንስፖርት አገልግሎቱን ለማስተጓጎል በሞከሩ አሽከርካሪዎች ላይ መንግስት ክትትል አድርጎ የእርምት እርምጃ መውሰድ በመጀመሩ እንግልቱ ከመቅረቱ ባለፈ በተቀመጠው የታሪፍ ክፍያ መጓዝ እንደቻሉ ገልጸዋል።
አስተያየታቸውን የሰጡ አሽከርካሪዎችም በኩፖን በሚቀዱት ነዳጅ በተቀመጠው ታሪፍ መሰረት የትራንስፖርት አገልግሎት እየሰጡ መሆናቸውን ተናግረዋል።
በከተማው ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ መምሪያ ነዳጅ በተራና በኩፖን የሚቀዱበት ሁኔታ መመቻቸቱ ችግሩን እያቃለለው መምጣቱን ገልጸው፣ ህገወጥ ተግባር በሚፈጽሙ አሽከርካሪዎች ላይ በተጀመረው ክትትልና ቁጥጥር ደስተኛ መሆናቸውን ተናግረዋል።
የወላይታ ሶዶ ከተማ ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ መምሪያ ኃላፊ መቅደስ በዛብህ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ወቅታዊውን የነዳጅ እጥረት ምክንያት በማድረግ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎትን ለማስተጓጎል በሞከሩ አካላት ላይ ክትትል በማድረግ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን ተናግረዋል።

ከወላይታ ሶዶ መናኸሪያ በ62 የስምሪት መስመሮች የሚነሱ ከ1 ሺህ 500 በላይ ተሽከርካሪዎች ነዳጅ በኩፖን እንዲቀዱ መደረጉን ገልጸዋል።
በህግ አግባብ የማይንቀሳቀሱትን ለተወሰነ ጊዜ ከስምሪት የማስወጣትና በገንዘብ የሚቀጡበት ስርዓት መዘርጋቱን ገልጸው፣ በኩፖን የቀዱትን ነዳጅ ለታለመለት ዓላማ ያላዋሉ አሽከርካሪዎች መቀጣታቸውን ተናግረዋል።
በዚህም በአሁኑ ወቅት የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ላይ ሲስተዋል የነበረው ችግር እየተፈታ መምጣቱን ገልጸው፣ ክትትሉ ይጠናከራል ብለዋል።

የወላይታ ሶዶ ከተማ ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ኮማንደር ሀብታሙ አሰፋ በበኩላቸው እንደገለጹት፤ በተለያዩ ማደያዎች ጨለማን ተገን በማድረግ በህገ ወጥ መንገድ ነዳጅ ሲሸጡ የተገኙ ከአምስት በላይ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ ተጀምሯል።
እንዲሁም ከህግ ውጭ ሲዘዋወር የነበረ 9ሺህ 700 ሊትር በላይ ናፍጣ እና 2 ሺህ 259 ሊትር በላይ ቤንዚን ተይዞ ለመንግስት ገቢ መደረጉን ገልጸው፣ ነዋሪው ህገወጥ ድርጊትን በመከላከል እያደረገ ያለውን ተሳትፎ አድንቀዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026