የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

 በዞኑ እየተካሔደ ያለው የኮሪደር ልማት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል

Jul 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጎንደር፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በማእከላዊ ጎንደር ዞን የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የዞኑ ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ አስታወቀ።

የመምሪያው የ2018 ዓ.ም የእቅድ አፈፃፀም ግምገማና የ2019 ዓ.ም እቅድ ትውውቅ መድረክ በጎንደር ከተማ ዛሬ ተካሒዷል።

የመምሪያ ኃላፊው አቶ ገድፍ ጌትነት በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፤ የለውጡ መንግስት አሻራ የሆነው የኮሪደር ልማት ከተሞችን በማዘመን ተወዳዳሪ እንዲሆኑ እያደረገ ነው።


በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በዞኑ ስር በሚገኙ በአራት የከተማ አስተዳደሮችና በዘጠኝ መሪ ማዘጋጃ ቤት ከተሞች የኮሪደር ልማት ስራ ማከናወን መቻሉን ገልጸዋል።

ለኮሪደር ልማት ስራው ህብረተሰቡ ከ68 ሚሊዮን ብር በላይ አስተዋጽኦ በማድረግ ለልማት ያለውን ቁርጠኝነት ማረጋገጡን ገልጸዋል።

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎችን አጠናክሮ ከማስቀጠል ባለፈ፤በ2019 በጀት ዓመት የልማት ስራውን ወደ ሌሎች ከተሞች የማስፋፋት ስራ ትኩረት እንደሚሰጠው አንስተዋል።

ከተሞችን የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት ማዕከል ለማድረግ የተጀመረው የኮሪደር ልማት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ያሉት ደግሞ በብልጽግና ፓርቲ የዞኑ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፋሲል ሠንደቁ ናቸው።

ይህም ከተሞቹን በማዘመን ለነዋሪዎች፣ ለጎብኝዎችና ለንግድ የተመቹ ከማድረግ ባለፈ የክልሉን ገጽታ ለመገንባት ተደማሪ አቅም እንደሚሆኑ አስረድተዋል።

በዞኑ የአንባ ጊዮርጊስ ከተማ አስተዳደር ከተማና መሠረተ ልማት ፅህፈት ቤት ዋና ስራ አስኪያጅ ዲያቆን ወልዴ ባዘዘው እንደገለጹት ፤ የኮሪደር ልማቱ የማሕበረሰቡን አኗኗር ለማዘመን የሚያስችል ነው።

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በከተማ አስተዳደሩ በኮሪደር ልማት ሁለት ነጥብ አምስት ኪሎ ሜትር ደረጃውን የጠበቀ የሳይክልና የእግረኛ መንገድ መገንባት መቻሉን አመልክተዋል።


ሌላው የጎንደር ዙሪያ ወረዳ የማክሰኝት መሪ ማዘጋጃ ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ሙሉአለም ሙጨ በበኩላቸው፤ የኮሪደር ልማት ስራው ከተማዋን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያበረክት ነው ብለዋል።

በአዲሱ በጀት ዓመትም የኮሪደር ልማት ስራውን አጠናክሮ በማስቀጠል የከተማዋን እድገት ለማፋጠንና ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።

በመድረኩ ላይ በዞኑ የሚገኙ የከተማ አስተዳደሮች፣የወረዳ ከተማ አመራሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026