የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

 በዞኑ እየተካሔደ ያለው የኮሪደር ልማት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል

Jul 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጎንደር፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በማእከላዊ ጎንደር ዞን የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የዞኑ ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ አስታወቀ።

የመምሪያው የ2018 ዓ.ም የእቅድ አፈፃፀም ግምገማና የ2019 ዓ.ም እቅድ ትውውቅ መድረክ በጎንደር ከተማ ዛሬ ተካሒዷል።

የመምሪያ ኃላፊው አቶ ገድፍ ጌትነት በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፤ የለውጡ መንግስት አሻራ የሆነው የኮሪደር ልማት ከተሞችን በማዘመን ተወዳዳሪ እንዲሆኑ እያደረገ ነው።


በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በዞኑ ስር በሚገኙ በአራት የከተማ አስተዳደሮችና በዘጠኝ መሪ ማዘጋጃ ቤት ከተሞች የኮሪደር ልማት ስራ ማከናወን መቻሉን ገልጸዋል።

ለኮሪደር ልማት ስራው ህብረተሰቡ ከ68 ሚሊዮን ብር በላይ አስተዋጽኦ በማድረግ ለልማት ያለውን ቁርጠኝነት ማረጋገጡን ገልጸዋል።

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎችን አጠናክሮ ከማስቀጠል ባለፈ፤በ2019 በጀት ዓመት የልማት ስራውን ወደ ሌሎች ከተሞች የማስፋፋት ስራ ትኩረት እንደሚሰጠው አንስተዋል።

ከተሞችን የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት ማዕከል ለማድረግ የተጀመረው የኮሪደር ልማት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ያሉት ደግሞ በብልጽግና ፓርቲ የዞኑ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፋሲል ሠንደቁ ናቸው።

ይህም ከተሞቹን በማዘመን ለነዋሪዎች፣ ለጎብኝዎችና ለንግድ የተመቹ ከማድረግ ባለፈ የክልሉን ገጽታ ለመገንባት ተደማሪ አቅም እንደሚሆኑ አስረድተዋል።

በዞኑ የአንባ ጊዮርጊስ ከተማ አስተዳደር ከተማና መሠረተ ልማት ፅህፈት ቤት ዋና ስራ አስኪያጅ ዲያቆን ወልዴ ባዘዘው እንደገለጹት ፤ የኮሪደር ልማቱ የማሕበረሰቡን አኗኗር ለማዘመን የሚያስችል ነው።

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በከተማ አስተዳደሩ በኮሪደር ልማት ሁለት ነጥብ አምስት ኪሎ ሜትር ደረጃውን የጠበቀ የሳይክልና የእግረኛ መንገድ መገንባት መቻሉን አመልክተዋል።


ሌላው የጎንደር ዙሪያ ወረዳ የማክሰኝት መሪ ማዘጋጃ ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ሙሉአለም ሙጨ በበኩላቸው፤ የኮሪደር ልማት ስራው ከተማዋን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያበረክት ነው ብለዋል።

በአዲሱ በጀት ዓመትም የኮሪደር ልማት ስራውን አጠናክሮ በማስቀጠል የከተማዋን እድገት ለማፋጠንና ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።

በመድረኩ ላይ በዞኑ የሚገኙ የከተማ አስተዳደሮች፣የወረዳ ከተማ አመራሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

 በዞኑ እየተካሔደ ያለው የኮሪደር ልማት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል

ጎንደር፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በማእከላዊ ጎንደር ዞን የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የዞኑ ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ...

Jul 23, 2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8/2018 ( አዜአ) ፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ኤሎምቢ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።...

Jul 16, 2026

ኢትዮጵያ የቀጣናውን የኃይል ትስስር ይበልጥ በማጠናከር የዲፕሎማሲና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነቷን ለማረጋገጥ እየሰራች ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የቀጣናውን የኃይል ትስስር ይበልጥ በማጠናከር የዲፕሎማሲና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነቷን ለማረጋገጥ እየሰራች መሆኑን ...

Jul 8, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ-ዘርፍ ኢኮኖሚ ትግበራ ምርታማነትን በማሻሻል የዘርፎችን ውጤታማነት አሳድጓል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የተከተለችው የብዝኅ-ዘርፍ ኢኮኖሚ ትግበራ ስኬታማ የሪፎርም ሥራዎች ምርታማነትን በማሳደግ የዘርፎችን ውጤታማነ...

Jul 8, 2026