የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

Aug 31, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወጣት ይኖርብናል ሲሉ የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቀጣይ አምስት ዓመትና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ በየደረጃው ባሉ የከተማ አስተዳደሩ የሥራ ኃላፊዎች ውይይት እየተደረገበት ነው።


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚህ ወቅት እንዳሉት፣ ሕዝባችን ያለፈውን ስትራቴጂያዊ ዕቅድ በሚገባ በመፈጸማችን ለቀጣዩ አምስት ዓመታት በድጋሚ እንድናገለግል ድምፁን ሰጥቶናል።


በመሆኑም በቀጣዩ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈጻጸማችንን በማሳደግ፣ ሕዝባችን የሰጠንን ኃላፊነት በብቃት መወጣት ይኖርብናል ብለዋል።


ከ2019 እስከ 2023 በሚተገበረው የአምስት ዓመቱ ስትራቴጂክ ዕቅድ ላይ ሁሉም አመራር የጠራ ግንዛቤ ኖሮት፣ የከተማዋን የብልጽግና ራዕይ የማሳካት የሕዝብ ኃላፊነት እንዳለበት ገልጸዋል።


ሕዝቡ አምኖ እንደገና እንደመረጣቸው የገለጹት ከንቲባ አዳነች፣ የሥራ ባህላችንን በማሳደግ ለዜጎች የገባነውን ቃል የምንፈጽምበት ነው ብለዋል።


ቀጣይነትን መሠረት ያደረገ የሥራ ባህልን ማሳደግና ያለፉ ድክመቶችን በማረም፣ ጥንካሬዎችን በማስቀጠል የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን ማሳለጥ እንደሚገባ ገልጸዋል።


በዕቅዳችን ላይ ተግባቦት መፍጠርና የተግባባንበትን በብቃት መፈጸም ይጠበቅብናል ብለዋል።


በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይን በተባበረ ክንድ የማሳካት ተግባር ተጨባጭ ውጤት ማምጣት እንዳስቻለ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026

በዞኑ የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ አጠናቆ ወደ ስራ ለማሰገባት አስችሏል

አምቦ፤ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እን...

Jul 24, 2026