የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

Aug 17, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገለጹ።

የተጠናቀቀው በጀት ዓመት አፈፃፀምና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ የክልል፣ የዞንና የወረዳ የሥራ ኃላፊዎች የተገኙበት የውይይት መድረክ በሰመራ ተካሄዷል።


በውይይት መድረኩ ማጠቃለያ ላይ የተገኙት ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ እንደተናገሩት፣ የክልሉን ልማት ለማቀላጠፍና የህብረተሰብ ጥያቄዎችን ለመመለስ ገቢን በአግባቡ መሰብሰብ ከፍተኛ ሚና አለው።

ርዕሰ መስተዳድሩ አክለውም፣ በተያዘው በጀት ዓመት በክልሉ የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።

ከዓመት ወደ ዓመት ገቢን የመሰብሰብ አቅም እየጨመረ መምጣቱን ገልጸው፣ ከለውጡ በፊት የነበረውን 790 ሚሊዮን ብር በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ወደ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ማሳደግ መቻሉን ተናግረዋል።

የመሰብሰብ አቅምን በማሳደግ በጀትን በራስ አቅም ለመሸፈን የሚደረገው ጥረት እየተጠናከረ መምጣቱን ገልጸው፣ በተለይም አመራሩ ኃላፊነቱን በአግባቡ ሊወጣ እንደሚገባ አሳስበዋል።

መተባበርንና መትጋትን ማዕከል በማድረግ የታቀደውን ዕቅድ ለማሳካት የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አብራርተዋል።

በያዝነው ዓመት ደግሞ የገቢ ግብርን ከፍ በማድረግ ከ16 ቢሊዮን ብር በላይ ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ስራ የተገባ መሆኑን ገልጸው፣ ለዚህ ስራ ስኬታማነት በየደረጃው ያለው አመራር የድርሻውን መወጣት እንዳለበትም አስገንዝበዋል።

በተያዘው በጀት ዓመት ገቢን አሟጦ በመሰብሰብ ለሕዝብ የልማት ጥያቄዎች ምላሽ የመስጠቱ ተግባርን ማጠናከር ከሁላችንም ይጠበቃል ያሉት ደግሞ የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ አቶ አወል አብዱ ናቸው።

የሰመራ ሎጊያ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኢንጂነር አህመድ ኑር ሳሊም በበኩላቸው፣ የከተማዋን የገቢ አቅም የመለየት ስራዎች መከናወናቸውንና ለፈጻሚ ባለሙያዎች ትጥቅ የሚሆናቸው ስልጠናና የልምድ ልውውጥ መካሄዱንም በመድረኩ ገልጸዋል።


በመርሃ ግብሩ ማጠቃለያ ላይ ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ከተማ አስተዳደሮችና ወረዳዎች የእውቅና እና የሽልማት ስነ-ስርዓት አከናውነዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026

በዞኑ የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ አጠናቆ ወደ ስራ ለማሰገባት አስችሏል

አምቦ፤ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እን...

Jul 24, 2026

 በዞኑ እየተካሔደ ያለው የኮሪደር ልማት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል

ጎንደር፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በማእከላዊ ጎንደር ዞን የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የዞኑ ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ...

Jul 23, 2026