የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

Sep 11, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን በብልጽግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽህፈት ኃላፊ ኢሳቅ አብዱልቃድር ተናገሩ።

የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ጳጉሜን 5 (የነገ ቀን) ምክንያት በማድረግ በአሶሳ ከተማ የግራናይት ፋብሪካ እና የቀርከሃ ፋብሪካዎች የስራ እንቅስቃሴ ጎብኝተዋል።


በጉብኝቱ ላይ የተገኙት በብልጽግና ፓርቲ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ኢሳቅ አብዱልቃድር፤ በክልሉ የተጀመሩ ሁለንተናዊ የልማት ስራዎች ትልቅ ተስፋ የተሰነቀባቸው መሆኑን ገልጸዋል።

በጉብኝቱ ያረጋግጥነው ይህንኑ ነው ያሉት ሃላፊው በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል ብለዋል።

በክልሉ በተለይም ወጣቶች የስራ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑና በዲጂታል ቴክኖሎጂ የዳበረ እውቀት እንዲኖራቸው ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን አንስተዋል።

ባለፋት ዓመታት የተከናወኑ የልማት ስራዎች የነገዋን ኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ የሚያረጋግጡ መሆናቸውን እና የዜጎችን ተጠቃሚነት በተግባር ያሳዩ መሆናቸውንም ገልጸዋል።

በክልሉ የግብርናውን፣ ማዕድንና የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ቀጣይነት ያለው የኢኮኖሚ ዕድገት እየተመዘገበ እንደሆነም ተናግረዋል።


በመርሃ ግብሩ በክልሉ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ጉዞ እና የኢንቨስትመንት አማራጮችን ማልማት ላይ ያተኮረ የፓናል ውይይት ተካሂዷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026