የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው ልዩ ስብሰባ የተለያዩ የብድርና ድጋፍ ስምምነት አዋጆችን አጸደቀ

Jun 27, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው ልዩ ስብሰባ ከዓለም ዓቀፍ የልማት ማህበር ጋር የተፈረሙ ሶስት የፋይናንስ ድጋፍና ብድር ስምምነት አዋጆችን አጸደቀ፡፡

6ኛው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ ልዩ ስብሰባ በዛሬው እለት ተካሂዷል።


ለምክር ቤቱ ከቀረቡት ስምምነቶች መካከል የመጀመሪያው ለዘላቂ እና ሁሉን አቀፍ የእድገት ልማት ፖሊሲ ማስፈፀሚያ የሚውል የአራት መቶ ሰላሳ ሰባት ሚሊዮን አራት መቶ ሺ (437,400,000) ኤስ.ዲ.አር የብድር ስምምነት ነው፡፡

ሁለተኛው የማህበረሰብ ተኮር የመሬት አያያዝ ፕሮግራም ማስፈፀሚያ የሚውል የአንድ መቶ አርባ አምስት ሚሊዮን አምስት መቶ ሺ (145,500,000) ኤስ.ዲ.አር የብድር ስምምነት ነው፡፡

ሶስተኛው ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የመስኖ ልማት ለዘላቂ ምርታማነት ፕሮጀክት ማስፈፀሚያ የሀምሳ አራት ሚሊዮን ስድስት መቶ ሺ (54,600,000) ኤስ.ዲ.አር የብድር ስምምነት ነው፡፡

ምክር ቤቱም እነኚህን የብድርና ድጋፍ ስምምነት አዋጆችን መርምሮ አጽድቋል።


የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ በዚሁ ወቅት፤ የብድርና ድጋፍ ስምምነቶች ኢትዮጵያ የምታከናውናቸው የልማት ተግባራት ምን ያክል ለውጥ እያመጡ እና የህብረተሰቡን ህይወት በተጨባጭ እየቀየሩ መሆናቸውን የሚያሳዩ ናቸው ብለዋል።

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ሪፎርሙን ይበልጥ በማጠናከር፤ ወደ ውጪ የሚላኩ ምርቶችን በመጠንና በጥራት በማሳደግ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ለማግኘት አይነተኛ ሚና እንደሚኖራቸው ገልጸዋል።

የወጣቶችን፣ ሴቶችን፣ የአርሶና አርብቶ አደሮችን ህይወት ለማሻሻል በሚደረገው ረብርብ ትልቅ የፋይናንስ አቅም እንደሚሆን ጠቁመዋል።

የአየር ንብረት ለውጥን በመከላከል አረንጓዴ ኢኮኖሚን ለመገንባትና የመስኖ ልማቶችን ለማዘመን እንደሚያግዝም እንዲሁ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በማስፋፋት የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የባለድርሻ አካላት ድጋፍ ሊጠናከር ይገባል 

ጋምቤላ፤ ሰኔ 18/2018 (ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በማስፋፋት የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ለተያዘው ግብ መሳካት፣ የባለድ...

Jun 26, 2026

አዲሱ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ፣ ከአዲስ አበባ 40 ኪ.ሜ ርቀት ላይ፣ ከባሕር ጠለል በላይ በ1,910 ሜትር ከፍታ ላይ እየተገነባ ይገኛል

‎አዲስ አበባ፤ ሰኔ 8/2018 (ኢዜአ)፦አዲሱ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ፣ ከአዲስ አበባ 40 ኪ.ሜ ርቀት ላይ፣ ከባሕር ጠለል በላይ በ1,910 ...

Jun 16, 2026

በክልሉ ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ ነው-ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ

ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

May 21, 2026

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026